በኢየሱስ ክርስቶስ ታምናለህ; እንዴት?
በዘመናችን በክርስትና ስም ክርስቲያን ተብለው የሚጠሩ በጣም ብዙ ናቸው:: ክርስትና ማለትግን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የተጠመቀ የክርስቶስ ተከታይ እና በክርስቶስ የሚያምን ማለት ነው ::
በክርስቶስ ማመንም፦
ሀ)የአብ የባህሪ ልጅ ነው ብሎ ማመን፡፡
እግዚአብሔር አምላካችን የስም፣የአካል ሦስትነት አለው። በግብር ሶስትነት ፦
አብ ወላዲ ነው ወልድን፤
ወልድ ተወላዲ ነው ከአብ የሚወለድ ፤
መንፈስ ቅዱስ ሰራፂ (ከአብ የወጣ) ነው፤
ይህ ማለት ግን አብ ወልድንና መንፈስ ቅዱስን በዘመን አይቀድማቸውም። በክብሩም አይበልጣቸውም። አብ አባት ስለሆነም አስቀድሞ በዮርዳኖስ በኋላም በደብረታቦር “ . . . በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጀ ይህ ነው ” አለ:: ማቴ ፲፯፦፭
ለ)የባህሪ አምላክ ብሎ ማመን ማመን
ኢየሱስ ክርስቶስ የባህሪ አምላክ ነው (፩ኛ ዮሐ ፭፦፳ ) ቅዱስ ጳውሎስም ስለ ክርስቶስ የባህሪ አምላክነት ሲገልጽፅ “ . . . ከሁሉ በላይ ሆኖ ለዘላለም የተባረከ አምላክ ነው” ብሏል:: ሮሜ ፱፦፭ አምላክነቱም የባህሪው ስለሆነ ለቅዱሳን የጸጋ (የስጦታ ) አምላክ ይሆን ዘንድ ይሰጣል(ይሾማል ) እንጂ እርሱ ከማንም አይቀበልም::
ሐ) እግዚአብሔር ነው ብሎ ማመን ፤
የእግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር ነው:: ይህንን እንደሚከተለው እንመለከታለን:: አስቀድሞ ኢዩኤል ነቢይ ” . . . የእግዚአብሔር ስም የሚጠሩ ይድናሉ”:: ብሎ ነበር :: ቅዱስ ጴጥሮስም “ የጌታ ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል:: “ ኢዩ ፸፦ ፴፪ የሐዋ ፸:_፳፮ ብሎ ተናገረ :: ጌታ የተባለ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው :: ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር ስለሆነ “. . . የእግዚአብሔር ስም የሚለውን የጌታ ስም ብሎ ደገመው “ :: እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ አረገ “ :: መዝ ፵፮(፵፯)፦፮ ይላል ነብየ እግዚአብሔር ዳዊት: : በእግዚአብሔር መውጣት መውረድ፡ መቀመጥ መነሳት የለበትም በአለም ምሉዕ (ምሉዕ በኩለኄ) ነውና : : የመድሀኒዓለም እርገት ሲነገር ነውና የሐዋ ፮፦፱
እግዚአብሔር ግልፅ ሆኖ ይመጣል የሚለውም ” እናንተ የገሊላ ሰዎች ሆይ ወደ ሰማይ እያያችሁ ለምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ ያረገው ኢየሱስ ከእናንተ ወደ ሰማይ ሲያርግ እንዳያችሁት እንዲሁ ዳግመኛ ይመጣል” አላቸው መዝ ፵፬(፭)፤ የሐዋ ፩፦፲፩ ብለው የሚመጣ እግዚአብሔር እንደሆነ አስተምረዋል::
“ በመጀመሪያ ቃል ነበር ፡ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበር :ቃልም እግዚአብሔር ነበር : ብሎ ወንጌላዊው ዮሐንስ የቃልን (የኢየሱስ ክርስቶስን ) እግዚአብሔርነት ጽፏል:: ኢሳ ፵፦፫ ማቴ ፫፦፫
መ) ፈጣሪ ነው ብሎ ማመን
ለፍጥረቱ መድሀኒት ለመሆን የፈጠረውን ሰው ከዳቢሎስ ቁራኝነት ከወደቀበት ለማንሳት የመጣ ኢየሱስ ክርስቶስ የፍጥረት ሁሉ ፈጣሪ ነው:: ዩሐ ፩፦፫ ፤ መዝ ፴፪፦፮ ፈጣሪም ስለሆነ አማላጅ ሊሆን አይችልምና :: ምክናየቱም አማላጅ ሊሆን የሚችል ፍጡር ነውና ::
ሠ) ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በስልጣንና በህልውና አንድ መሆኑን ማመን
ስላሴ(አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ) በስልጣን በህልውና በባህሪ በፈቃድ ይህን ዓለም በማሳለፍ ይህን በመሳሰለው ነገር ሁሉ አንድ ናቸው:: (ዩሐ ፲፦፴ ፤ ዩሐ፲፬፦፲ )
ረ) የተዋሀደው የድንግል ማርያምን ስጋና ነፍስ ነው ብሎ ማመን
አካላዊ ቃል ከሰማይ ስጋና ነፍስን ይዞ አልመጣም (አልወረደም) :: ሰው የሆነ ከድንግልማርያምስጋና ነፍስ ነስቶ በተዋህዶ ነው:: በመሆኑም እመቤታችን ቅድስት ድንግልማርያም ወላዲተ አምላክ በድንግልና ፀንሳ በድንግልና የወለደች ትባላለች::
ሰ) ትንሳኤውን ያለጥርጥር ማመን
ለድህነት ዓለም የመጣ እግዚአብሔር ሞትን በሞቱ ድል አድርጎ ተነሳ ሲነሳም በስጋ ነው:: ማቴ ፳፰፦፭ ፤ ሉቃ ፳፬፤፫ ፤ሉቃ ፳፬፤፴፮
ሸ) ያረገው በስጋው መሆኑን ማመን
መድሀኒዓለም ሞትን ድል አድርጎ በተነሳ በ፵ኛው ቀን እጁን በመጫን(በአንብሮተ እድ ) ሐዋርያትን እስከ ፓትሪያርክነት ሾሟል :: እርሱንም እያዩት የእርቀት ያይደለ (ከፍ ከፍ እያለ ) ከፍፁም ምስጋና ፈፅሞ ወደ አልተለየው ወደ ባህሪ አባቱ አርጓል::ያረገውም በስጋና በነፍስ፣በአጥንትና በደም፣በስጋና በጅማት እንዳለ ነው:: ፩ኛ ጴጥ ፫፦፳፭
ቀ) ሲመጣ በስጋ ማርያም መሆኑን ማመን
በኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት ወቅት ለነበሩ ቤተሰቦች ቅዱሳን መላእክት እንደነገራቸውጌታችን ሲመጣ እየታየ በግልፅ ሆኖ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በነሳው (በተዋሃደው)ስጋ ነው :: መዝ ፵፱(፶)፦፪ ፤ የሐዋ ፮፦፲፩ ራዕ ዮሐ ፮፦፯
እንግዲህ ከላይ እንደተመለከትነው መፅሀፍ ቅዱስ የሚነግረን ቅዱሳን አባቶቻችን የሚያስተምሩን ኢየሱስ ክርስቶስ አማላጅ ሳይሆን ተማላጅ፣ አንድ አካል አንድ ባህሪ፣ ፍጡር ሳይሆን ፈጣሪ እንደ ሆነ ነው:: የዘላለም ሀይወትን ለማግኘት እንግዲህ አምነን በመግባት ቅዱስ ስጋውን ክቡር ደሙን መቀበል ይገባናል::
ወስብሀት ለእግዚአብሔር
በክርስቶስ ማመንም፦
ሀ)የአብ የባህሪ ልጅ ነው ብሎ ማመን፡፡
እግዚአብሔር አምላካችን የስም፣የአካል ሦስትነት አለው። በግብር ሶስትነት ፦
አብ ወላዲ ነው ወልድን፤
ወልድ ተወላዲ ነው ከአብ የሚወለድ ፤
መንፈስ ቅዱስ ሰራፂ (ከአብ የወጣ) ነው፤
ይህ ማለት ግን አብ ወልድንና መንፈስ ቅዱስን በዘመን አይቀድማቸውም። በክብሩም አይበልጣቸውም። አብ አባት ስለሆነም አስቀድሞ በዮርዳኖስ በኋላም በደብረታቦር “ . . . በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጀ ይህ ነው ” አለ:: ማቴ ፲፯፦፭
ለ)የባህሪ አምላክ ብሎ ማመን ማመን
ኢየሱስ ክርስቶስ የባህሪ አምላክ ነው (፩ኛ ዮሐ ፭፦፳ ) ቅዱስ ጳውሎስም ስለ ክርስቶስ የባህሪ አምላክነት ሲገልጽፅ “ . . . ከሁሉ በላይ ሆኖ ለዘላለም የተባረከ አምላክ ነው” ብሏል:: ሮሜ ፱፦፭ አምላክነቱም የባህሪው ስለሆነ ለቅዱሳን የጸጋ (የስጦታ ) አምላክ ይሆን ዘንድ ይሰጣል(ይሾማል ) እንጂ እርሱ ከማንም አይቀበልም::
ሐ) እግዚአብሔር ነው ብሎ ማመን ፤
የእግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር ነው:: ይህንን እንደሚከተለው እንመለከታለን:: አስቀድሞ ኢዩኤል ነቢይ ” . . . የእግዚአብሔር ስም የሚጠሩ ይድናሉ”:: ብሎ ነበር :: ቅዱስ ጴጥሮስም “ የጌታ ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል:: “ ኢዩ ፸፦ ፴፪ የሐዋ ፸:_፳፮ ብሎ ተናገረ :: ጌታ የተባለ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው :: ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር ስለሆነ “. . . የእግዚአብሔር ስም የሚለውን የጌታ ስም ብሎ ደገመው “ :: እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ አረገ “ :: መዝ ፵፮(፵፯)፦፮ ይላል ነብየ እግዚአብሔር ዳዊት: : በእግዚአብሔር መውጣት መውረድ፡ መቀመጥ መነሳት የለበትም በአለም ምሉዕ (ምሉዕ በኩለኄ) ነውና : : የመድሀኒዓለም እርገት ሲነገር ነውና የሐዋ ፮፦፱
እግዚአብሔር ግልፅ ሆኖ ይመጣል የሚለውም ” እናንተ የገሊላ ሰዎች ሆይ ወደ ሰማይ እያያችሁ ለምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ ያረገው ኢየሱስ ከእናንተ ወደ ሰማይ ሲያርግ እንዳያችሁት እንዲሁ ዳግመኛ ይመጣል” አላቸው መዝ ፵፬(፭)፤ የሐዋ ፩፦፲፩ ብለው የሚመጣ እግዚአብሔር እንደሆነ አስተምረዋል::
“ በመጀመሪያ ቃል ነበር ፡ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበር :ቃልም እግዚአብሔር ነበር : ብሎ ወንጌላዊው ዮሐንስ የቃልን (የኢየሱስ ክርስቶስን ) እግዚአብሔርነት ጽፏል:: ኢሳ ፵፦፫ ማቴ ፫፦፫
መ) ፈጣሪ ነው ብሎ ማመን
ለፍጥረቱ መድሀኒት ለመሆን የፈጠረውን ሰው ከዳቢሎስ ቁራኝነት ከወደቀበት ለማንሳት የመጣ ኢየሱስ ክርስቶስ የፍጥረት ሁሉ ፈጣሪ ነው:: ዩሐ ፩፦፫ ፤ መዝ ፴፪፦፮ ፈጣሪም ስለሆነ አማላጅ ሊሆን አይችልምና :: ምክናየቱም አማላጅ ሊሆን የሚችል ፍጡር ነውና ::
ሠ) ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በስልጣንና በህልውና አንድ መሆኑን ማመን
ስላሴ(አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ) በስልጣን በህልውና በባህሪ በፈቃድ ይህን ዓለም በማሳለፍ ይህን በመሳሰለው ነገር ሁሉ አንድ ናቸው:: (ዩሐ ፲፦፴ ፤ ዩሐ፲፬፦፲ )
ረ) የተዋሀደው የድንግል ማርያምን ስጋና ነፍስ ነው ብሎ ማመን
አካላዊ ቃል ከሰማይ ስጋና ነፍስን ይዞ አልመጣም (አልወረደም) :: ሰው የሆነ ከድንግልማርያምስጋና ነፍስ ነስቶ በተዋህዶ ነው:: በመሆኑም እመቤታችን ቅድስት ድንግልማርያም ወላዲተ አምላክ በድንግልና ፀንሳ በድንግልና የወለደች ትባላለች::
ሰ) ትንሳኤውን ያለጥርጥር ማመን
ለድህነት ዓለም የመጣ እግዚአብሔር ሞትን በሞቱ ድል አድርጎ ተነሳ ሲነሳም በስጋ ነው:: ማቴ ፳፰፦፭ ፤ ሉቃ ፳፬፤፫ ፤ሉቃ ፳፬፤፴፮
ሸ) ያረገው በስጋው መሆኑን ማመን
መድሀኒዓለም ሞትን ድል አድርጎ በተነሳ በ፵ኛው ቀን እጁን በመጫን(በአንብሮተ እድ ) ሐዋርያትን እስከ ፓትሪያርክነት ሾሟል :: እርሱንም እያዩት የእርቀት ያይደለ (ከፍ ከፍ እያለ ) ከፍፁም ምስጋና ፈፅሞ ወደ አልተለየው ወደ ባህሪ አባቱ አርጓል::ያረገውም በስጋና በነፍስ፣በአጥንትና በደም፣በስጋና በጅማት እንዳለ ነው:: ፩ኛ ጴጥ ፫፦፳፭
ቀ) ሲመጣ በስጋ ማርያም መሆኑን ማመን
በኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት ወቅት ለነበሩ ቤተሰቦች ቅዱሳን መላእክት እንደነገራቸውጌታችን ሲመጣ እየታየ በግልፅ ሆኖ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በነሳው (በተዋሃደው)ስጋ ነው :: መዝ ፵፱(፶)፦፪ ፤ የሐዋ ፮፦፲፩ ራዕ ዮሐ ፮፦፯
እንግዲህ ከላይ እንደተመለከትነው መፅሀፍ ቅዱስ የሚነግረን ቅዱሳን አባቶቻችን የሚያስተምሩን ኢየሱስ ክርስቶስ አማላጅ ሳይሆን ተማላጅ፣ አንድ አካል አንድ ባህሪ፣ ፍጡር ሳይሆን ፈጣሪ እንደ ሆነ ነው:: የዘላለም ሀይወትን ለማግኘት እንግዲህ አምነን በመግባት ቅዱስ ስጋውን ክቡር ደሙን መቀበል ይገባናል::
ወስብሀት ለእግዚአብሔር
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ