ማክሰኞ 24 ፌብሩዋሪ 2015

     ነገረ መለኮት (Theology)

<<Theology >> የሚለው ቃል ከሁለት የግሪክ ቃላት ማለትም ‹‹Theo›› እና ‹‹logy›› የተወሰደ ሲሆን ትርጓሜውም ‹‹ Theo›› ማለት ‹‹God›› ማለት ሲሆን ‹‹logy›› ደግሞ study or knowledge የሚል ቀጥተኛ ትርጉም አለው፡፡ በመሆኑም ‹‹Theology›› (የነገረ መለኮት) ማለት ስለ እግዚአብሔር የማይጨበጠውን፣የማይላጠውን፣ የማይገመተውን እንዲሁም ከሰዎች አእምሮ በላይ የሆነውን ጌትነቱንና አምላክነቱን መንፈስ ቅዱስ በገለጠላቸው መጠን ሰዎች የሚረዱበት ጥበብ ነው፡፡
እግዚአብሔር ተብሎ ወደ ግዕዝ የተተረጉመው በዕብራይስጡ ቋንቋ ኤል ወይም በብዙ ቁጥር ኤሎሄም የሚለው ቃል ነው፡፡ ኤል ማለት  ኃይል ማለት ነው፡፡ በታላቁ መጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ ሌሎች የእግዚአብሐር ስሞችም ይገኛሉ፡፡ ለምሳሌ ያህዌ ማለት የነበረ ያለና የሚኖር ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር የሚለው የግዕዝ ቃል ወደ አማርኛው ሲተረጎም የሀገር  ወይም የዓለም ጌታ ማለት ነው፡፡ በምድራችን ላይ በርካታ ሃይማኖቶች፤ እምነቶችና አመለካከቶች የመኖራቸውን ያህል ፍጥረታትን ሁሉ የፈጠረና (ያስገኘ) እና የየዕለት ሁኔታዎችን  የሚመራ እና  የሚቆጣጠር አንድ ከሰዎች በላይ የሆነ የማይታይ ትልቅ ኃይል ያለ መሆኑን አብዛኛው ወገኖች ይስማማሉ፡፡ ይሁን እንጂ እያንዳንዱ ሃይማኖት የራሱ የሆነ መመሪያና ትምህርት አለው፡፡
በዚህ መሰረት የክርስትና ነገረ መለኮት  ስንል ስለ እግዚአብሔር ህልውና ስለጠባዮቹ ስለመለኮታዊ አንድነቱ ሶስትነቱ ለፍጥረቱ ስለሚያደርገው ጥበቃ (መግበቱ) ከሶስቱ አካላት አንዱ እግዚአብሔር ወልድ በተለየ አካሉ ሰው ሆኖ ዓለምን ማዳኑንና በአጠቃላይም ለዚህ ሁሉ ትምህርት ምንጭ በሆነው አምላካዊ መጽሀፍ የተገለጸው ሃይማኖታዊ ሥርዓት የሚመረምር ትምህርት (ዕውቀት) ማለታችን ነው፡፡
መሆኑም በዚህች አጭር ፅሁፍ ውስጥ ይህንን ሀሳብ በስፋት ለማየት አባይን በጭልፋ ያህል ከባድ ስለሆነ በነገረ መለኮት ትምህርት ውስጥ በተለይ በኢትዮጵያ ኦርዶቶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለውን አስተምሮ በአጭሩ ለማየት እንሞክራለን፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ