ጸሎተ ፍትሐት
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስ ላይ የስድብ ቃል የሚናገር ሁሉ በዚህ ዓለምም ሆነ በሚመጣው ዓለም በደሉ ይቅር አይባልለትም ማለቱ በዚህ ዓለምና ለሚመጣው ዓለም ይቅር ሊባል የሚችልና ይቅር ሊባል የማይችል ሁለት የኃጢአት ዓይነት መኖሩን ይመላክተናል፡፡ (ማቴ፡-12÷32) በዚህ አባባል መሠረት በሚመጣው ዓለም ኃጢአት ይቅር የሚባል ከሆነ ጸሎተ ፍትሐት ጠቃሚ እንደሆነ እንገነዘባለን፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቶ ለነበረው ለኦኔሲፎር ‹‹በመጨረሻው ቀን ጌታ ምሕረትን ይሰጠው ›› ብሎ ጸልዮለታል (2ጢሞ፡-1÷18) ኦኔሲፎረም በሕይወት ያልነበረ መሆኑ የሚታወቀው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለሌሎች ሰላምታ ሲይቀርም ለእርሱ ግን የጸለየለት በመሆኑ ነው ለሞቱ ሰዎች መጸለይ የማያስፈልግና ጥቅም የሌለው ቢሆን ኖሮ ታላቁ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ለሞተ ሰው ባልጸለየ ነበር፡፡
(ለሞቱ ሰዎች መጸለይ (ጸሎተ ፍትሐት) በብሉይ ዘመንም የነበረ እንጂ በሐዲስ ኪዳን የተጀመረ አይደለም፡፡ ጀግናው መቃብዮስ በጦርነት ለሞቱ ወታደሮቹ የኃጢአት መስዋዕት ይደረግላቸው ዘንድ ሁለት ሺህ የብር ድራህማ አሰባስቦ ወደ ኢየሩሳሌም የላከ መሆኑን በ2ኛው መጽ.መቃ. 12÷43 ላይ ይጠቅሳል፡፡ የሐዋርያት ትምህርት የሆነው ዲድስቅልያ ‹‹...በጌታ ተስባስባችሁ ዘምሩላቸው በየአብያተ ክርስቲያናችሁ የቅዳሴ ጸሎት አድርጉ...›› (ዲድ አንቀጽ 33) በማለት ይገልጸዋል፡፡ የቅዱሳን ሞት በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው እንዲል ዘማሪው ዳዊት (መዝ 116÷115) በየአብያተ ክርስቲያናት በየዕለቱ በሚደረገው የቅዳሴ ጸሎት መካከል ለሙታን የሚጸለይ በመሆኑ ይህም ለሙታን የመጸለይ ሥርዓት ከጥንት ጀምሮ ሲሠራበት የኖረ መሆኑን ያስገነዝበናል፡፡
(.ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች በተላከው የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ላይ ባደረገው 41ኛው ስብከቱ፡- ‹‹...አንድ ሰው ኃጢአተኛ እንደሆነ ቢሞት የምንችለውን ያህል ልንረዳው ይገባል፡፡ የምንረዳውም በልቅሶና በኃዘን ሳይሆን በጸሎት በምጽዋትና በቁርባን ነው፡፡ የዓለምን ኃጢአት ወደተሸከመው የእግዚአብሔር በግ ስለሙታን የምንጸልየው እነርሱ መጽናናትን ዕረፍትን እንዲያገኙ ብለን ነው እንጂ በከንቱ አይደለም፡፡ ጻድቁ ኢዮብ ስለልጆቹ ያቀርብ የነበረው ቁርባን ጠቀሜታ ከነበረው ስለሙታን የምናቀርበው ቁርባን ምንኛ የበለጠ ጠቀሜታ ይኖረው?›› በማለት ገልጾታል፡፡ (የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ትምህርተ መለኮት 3ኛ መጽሐፍ ገጽ 508-509 በሚካኤል ሚና)
(.ነፍስ ከሥጋ እንደተለየች የመጨረሻ ዋጋዋን የምትቀበለው ወዲያው ሳይሆን በዕለተ ምጽአት በመሆኑ ለሰው ልጅ ሁሉ ተስፋ መንግስተ ሰማያትን ልዑለ ባሕርይ እግዚአብሔር አምላክ ያወርሳቸው ዘንድ በሕይወት ለሌሉ ክርስቲያኖች ሁሉ በእምነት በመሆን የፍትሐት ጸሎትን እናደርግላቸዋለን ፡፡
ታላቅ ጠቀሜታ አለውና (ፍትሐ ነገሥት አንቅጽ 22 ) በዚህ መሠረት ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ለሙታን የጸሎት ፍትሐት ሥርዓት በአግባቡ ትፈጽማለች፡፡
ሦስቱ የቅድስና መንገዶች በመባል የሚታወቁት ጥምቀት፣ ሥራና ሹመት ናቸው፡፡ እንደአለቃ አያሌው ታምሩ አገላለጽ የሰው ልጅ የቅድስና መንገዶች ከሦስቱ ውጭ እንደማይሆኑ ይጠቁሙናል፡፡ ቀጥሎም በተናጠል ለመመልከት እንሞክራለን፤
ሀ/ ቅድስና በጥምቀት፡- በጥምቀት ልጅነት ማግኘት የእግዚአብሔር ልጅ በሥጋ የሰው ልጅ ስለሆነ በእርሱ ሰጭነት በእርሱ ቤዛነት የሰው ልጅ ደግሞ በጸጋ በእግዚአብሔር ልጅ ይሆን ዘንድ ደግሞ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ መወለድ ነውና የእግዚአብሔር ልጅ በሥጋ የሰው ልጅ ስለሆነ በእርሱ ሰጭነት በእርሱ ቤዛነት የሰው ልጅ ደግሞ በጸጋ የእግዚአብሔር ልጅ ይሆን ዘንድ ደግሞ ከውኃና ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ይወለድ ዘንድ አስፈልጐታል በጥምቀት፡፡ (1ኛ ቆሮ፡- 1÷2፣ ኤፌ፡- 1÷1)
ለ/ ቅድስና በሥራ፡- ሰውነትን ለእግዚአብሔር በመለየት ፣ በስሙ ለተቀበሉት እምነት መስዋዕት አድርጐ በመስጠት የሚገኝ ቅድስና ነው፡፡ ለእግዚአብሔር የተሰጡ ፣ ለእግዚአብሔር የሆኑ፣ ለእግዚአብሔር የተለዩ ሁሉ በብሉይ ኪዳን ናዝራዊያን ይባሉ ነበር፤ ለምሳሌ፡- መስፍኑ ሶሞሶን ይጠቀሳል፡፡ (መጽ.ምሣሌ፡- 13÷5) በዚህ ስም በሐዲስ ኪዳንም ጌታችንም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ተጠርቶበታል፡፡ (ማቴ፡- 2÷23) ይህንን መሠረት በማድረግ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹...የጠራችሁ ቅዱስ እንደሆነ እናንተም በሥራችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ›› (1ኛ ጴጥ. 1÷15) በማለት መልእክቱን ጽፏል፡፡
ሐ/ የቅድስና ጸጋ በሹመት፡- በክርስትና የእግዚአብሔር ልጅ ለመሆን የታደሉ ክርስቲያኖች በእምነታቸው በምግባራቸው ከሚያገኙት ጸጋ ሌላ አሁንም በእምነታቸው፣ በምግባራቸው መልካምነት ተመርጠው በሹመት የሚገኙት ቅድስና አለ፡፡ አብ የመረጠውና የቀደሰው ወልድ ለሰው ያሰበውን የፈቀደውን ቤዛነት ሥራ በሞት ካተመ በትንሣኤው ከደመደመ በኋላ በሹመት የሚያገኘውን ከፍተኛውን ሥልጣንና ቅድስና ለመረጣቸው ለጠራቸው እርሱን እንዲመስሉ ለአዘጋጃቸው ለሰው ልጆች ሰጥቷል፡፡ ይህም ሥልጣን ማጥመቅ፣ ለማሰር፣ ለመፍታት፣ ተአምራትን ለማድረግ፣ ለመሾም፣ ለመሻር፣ ኃጢአትን ለማስተሰረይ፣ ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባት /ለማውጣት/ መስዋዕት ለማቅረብ የቅድስና ሹመት ሰጥቷቸዋል፡፡ (ዮሐ፡- 17÷17-20፡ ማቴ፡- 28÷18-20፣ ማር፡- 16÷15-20፣ ሉቃ፡- 24÷49-53)
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስ ላይ የስድብ ቃል የሚናገር ሁሉ በዚህ ዓለምም ሆነ በሚመጣው ዓለም በደሉ ይቅር አይባልለትም ማለቱ በዚህ ዓለምና ለሚመጣው ዓለም ይቅር ሊባል የሚችልና ይቅር ሊባል የማይችል ሁለት የኃጢአት ዓይነት መኖሩን ይመላክተናል፡፡ (ማቴ፡-12÷32) በዚህ አባባል መሠረት በሚመጣው ዓለም ኃጢአት ይቅር የሚባል ከሆነ ጸሎተ ፍትሐት ጠቃሚ እንደሆነ እንገነዘባለን፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቶ ለነበረው ለኦኔሲፎር ‹‹በመጨረሻው ቀን ጌታ ምሕረትን ይሰጠው ›› ብሎ ጸልዮለታል (2ጢሞ፡-1÷18) ኦኔሲፎረም በሕይወት ያልነበረ መሆኑ የሚታወቀው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለሌሎች ሰላምታ ሲይቀርም ለእርሱ ግን የጸለየለት በመሆኑ ነው ለሞቱ ሰዎች መጸለይ የማያስፈልግና ጥቅም የሌለው ቢሆን ኖሮ ታላቁ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ለሞተ ሰው ባልጸለየ ነበር፡፡
(ለሞቱ ሰዎች መጸለይ (ጸሎተ ፍትሐት) በብሉይ ዘመንም የነበረ እንጂ በሐዲስ ኪዳን የተጀመረ አይደለም፡፡ ጀግናው መቃብዮስ በጦርነት ለሞቱ ወታደሮቹ የኃጢአት መስዋዕት ይደረግላቸው ዘንድ ሁለት ሺህ የብር ድራህማ አሰባስቦ ወደ ኢየሩሳሌም የላከ መሆኑን በ2ኛው መጽ.መቃ. 12÷43 ላይ ይጠቅሳል፡፡ የሐዋርያት ትምህርት የሆነው ዲድስቅልያ ‹‹...በጌታ ተስባስባችሁ ዘምሩላቸው በየአብያተ ክርስቲያናችሁ የቅዳሴ ጸሎት አድርጉ...›› (ዲድ አንቀጽ 33) በማለት ይገልጸዋል፡፡ የቅዱሳን ሞት በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው እንዲል ዘማሪው ዳዊት (መዝ 116÷115) በየአብያተ ክርስቲያናት በየዕለቱ በሚደረገው የቅዳሴ ጸሎት መካከል ለሙታን የሚጸለይ በመሆኑ ይህም ለሙታን የመጸለይ ሥርዓት ከጥንት ጀምሮ ሲሠራበት የኖረ መሆኑን ያስገነዝበናል፡፡
(.ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች በተላከው የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ላይ ባደረገው 41ኛው ስብከቱ፡- ‹‹...አንድ ሰው ኃጢአተኛ እንደሆነ ቢሞት የምንችለውን ያህል ልንረዳው ይገባል፡፡ የምንረዳውም በልቅሶና በኃዘን ሳይሆን በጸሎት በምጽዋትና በቁርባን ነው፡፡ የዓለምን ኃጢአት ወደተሸከመው የእግዚአብሔር በግ ስለሙታን የምንጸልየው እነርሱ መጽናናትን ዕረፍትን እንዲያገኙ ብለን ነው እንጂ በከንቱ አይደለም፡፡ ጻድቁ ኢዮብ ስለልጆቹ ያቀርብ የነበረው ቁርባን ጠቀሜታ ከነበረው ስለሙታን የምናቀርበው ቁርባን ምንኛ የበለጠ ጠቀሜታ ይኖረው?›› በማለት ገልጾታል፡፡ (የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ትምህርተ መለኮት 3ኛ መጽሐፍ ገጽ 508-509 በሚካኤል ሚና)
(.ነፍስ ከሥጋ እንደተለየች የመጨረሻ ዋጋዋን የምትቀበለው ወዲያው ሳይሆን በዕለተ ምጽአት በመሆኑ ለሰው ልጅ ሁሉ ተስፋ መንግስተ ሰማያትን ልዑለ ባሕርይ እግዚአብሔር አምላክ ያወርሳቸው ዘንድ በሕይወት ለሌሉ ክርስቲያኖች ሁሉ በእምነት በመሆን የፍትሐት ጸሎትን እናደርግላቸዋለን ፡፡
ታላቅ ጠቀሜታ አለውና (ፍትሐ ነገሥት አንቅጽ 22 ) በዚህ መሠረት ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ለሙታን የጸሎት ፍትሐት ሥርዓት በአግባቡ ትፈጽማለች፡፡
ሦስቱ የቅድስና መንገዶች በመባል የሚታወቁት ጥምቀት፣ ሥራና ሹመት ናቸው፡፡ እንደአለቃ አያሌው ታምሩ አገላለጽ የሰው ልጅ የቅድስና መንገዶች ከሦስቱ ውጭ እንደማይሆኑ ይጠቁሙናል፡፡ ቀጥሎም በተናጠል ለመመልከት እንሞክራለን፤
ሀ/ ቅድስና በጥምቀት፡- በጥምቀት ልጅነት ማግኘት የእግዚአብሔር ልጅ በሥጋ የሰው ልጅ ስለሆነ በእርሱ ሰጭነት በእርሱ ቤዛነት የሰው ልጅ ደግሞ በጸጋ በእግዚአብሔር ልጅ ይሆን ዘንድ ደግሞ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ መወለድ ነውና የእግዚአብሔር ልጅ በሥጋ የሰው ልጅ ስለሆነ በእርሱ ሰጭነት በእርሱ ቤዛነት የሰው ልጅ ደግሞ በጸጋ የእግዚአብሔር ልጅ ይሆን ዘንድ ደግሞ ከውኃና ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ይወለድ ዘንድ አስፈልጐታል በጥምቀት፡፡ (1ኛ ቆሮ፡- 1÷2፣ ኤፌ፡- 1÷1)
ለ/ ቅድስና በሥራ፡- ሰውነትን ለእግዚአብሔር በመለየት ፣ በስሙ ለተቀበሉት እምነት መስዋዕት አድርጐ በመስጠት የሚገኝ ቅድስና ነው፡፡ ለእግዚአብሔር የተሰጡ ፣ ለእግዚአብሔር የሆኑ፣ ለእግዚአብሔር የተለዩ ሁሉ በብሉይ ኪዳን ናዝራዊያን ይባሉ ነበር፤ ለምሳሌ፡- መስፍኑ ሶሞሶን ይጠቀሳል፡፡ (መጽ.ምሣሌ፡- 13÷5) በዚህ ስም በሐዲስ ኪዳንም ጌታችንም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ተጠርቶበታል፡፡ (ማቴ፡- 2÷23) ይህንን መሠረት በማድረግ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹...የጠራችሁ ቅዱስ እንደሆነ እናንተም በሥራችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ›› (1ኛ ጴጥ. 1÷15) በማለት መልእክቱን ጽፏል፡፡
ሐ/ የቅድስና ጸጋ በሹመት፡- በክርስትና የእግዚአብሔር ልጅ ለመሆን የታደሉ ክርስቲያኖች በእምነታቸው በምግባራቸው ከሚያገኙት ጸጋ ሌላ አሁንም በእምነታቸው፣ በምግባራቸው መልካምነት ተመርጠው በሹመት የሚገኙት ቅድስና አለ፡፡ አብ የመረጠውና የቀደሰው ወልድ ለሰው ያሰበውን የፈቀደውን ቤዛነት ሥራ በሞት ካተመ በትንሣኤው ከደመደመ በኋላ በሹመት የሚያገኘውን ከፍተኛውን ሥልጣንና ቅድስና ለመረጣቸው ለጠራቸው እርሱን እንዲመስሉ ለአዘጋጃቸው ለሰው ልጆች ሰጥቷል፡፡ ይህም ሥልጣን ማጥመቅ፣ ለማሰር፣ ለመፍታት፣ ተአምራትን ለማድረግ፣ ለመሾም፣ ለመሻር፣ ኃጢአትን ለማስተሰረይ፣ ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባት /ለማውጣት/ መስዋዕት ለማቅረብ የቅድስና ሹመት ሰጥቷቸዋል፡፡ (ዮሐ፡- 17÷17-20፡ ማቴ፡- 28÷18-20፣ ማር፡- 16÷15-20፣ ሉቃ፡- 24÷49-53)
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ