ሐሙስ 26 ፌብሩዋሪ 2015

እመቤታችን ሆይ የሚለው ፀሎት ከየት መጣ
አንድ እህቴ እንዲህ በማለት ጥያቄ
ጠየቀቺኝ እናተ ኦርቶዶክሶች ስትፀልዩ
አባታችን ሆይ ካላቹ በሀላ እመቤታችን
ብላቹ እምትፀልዩት ፀሎት
ፍፁም ከመፅኀፍ ቅዱስ ውጪ ነው
ስለዚህ መፀለይ የለበትም አለቺኝ

.
.
እንግዲህ እኛም ተዋህዶ እንዳስተማረችን
የተወደደች እናታችንን
እንዲህ እያልን ከቃሉ ሳንወጣ በፀሎታችን
እንጠራታለን
እንዲህም እንላለን፦
.
እመቤታችን ንፅህት
ቅድስት ድንግል (ማቴ1:23)
ማሪያም ሆይ(2ቆሮ11:2)
በመልአኩ በቅድስ ገብርኤል ሰላምታ
ሰላም እንልሻለን (ሉቃ1:28)
በሀሳብሽ ድንግል ነሽ (2ቆሮ11:2
ንፅህት )
በሥጋሽም ድንግል ነሽ(ማቴ1:23)
(ህዝ44:2)
ያሸናፊ የልዑል እናት ሆይ (ሉቃ1:35)
ሰላምታ ላንች ይገባሻል
ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ አንች የተባረክሽ ነሽ
(ሉቃ1:28 ናሉቃ1:32)
የማህፀንሽ ፍሬ የተባረከ ነው (ሉቃ1:32)
ፀጋን የተመላሽ ቅድስት ሆይ ደስ ይበልሽ
ልዑል እግዚአብሔር ካንች ጋር ነውና
(ሉቃ1:28-30)
ከተወደደው ከልጅሽ ከጌታችን
ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ
ይቅርታና ምህረትን ለምኝልን
በቆሮ5:20
በፅድቅ ስራ የኖሩት ይለምኑ ዘንድ
ተሰጥቷቸዋልና
ሃጢአታችንምያስተሰርይ ዘንድ ለዘላለሙ
አሜን።
.
.
እኛም ይህን ከመፀለይ ቸል ብለን
የእናታችንን ውለታ አንረሳም፡፡
ነገር ግን ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ተዋህዶን
ሊተቹ የሚነሱትን እግዚአብሔር ልቦና
ይስጣቸው፡፡ አሜን፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ