ማክሰኞ 17 ማርች 2015





 
 ‹‹እርሱም መልሶ፦ ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር አልተላክሁም አለ።››
                የማቴዎስ ወንጌል 15፡24/ይድረስ ለአህዛብ/
ብዙ ጊዜ መሀመዳውያን ይህንን የጌታችንን ንግግር በመያዝ ኢየሱስ የተላከው ለእስራኤላውያን ብቻ ነው ይላሉ እስቲ አብረን ጥቅሱን እንመልከተው፡-
በመጀመሪያ ደረጃ እስራኤል ማለት ኤሁዳውያን ብቻ አይደሉም እኛ የሀዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች እስራኤል ዘነፍስ ተብለን እንጠራለን፡፡ከእስራኤል ቤት የጠፉት በጎች ሲል ጥቁስን ብቻውን ከወንጌላቱ የታሪክ አውድ (context)ነጥለን ስናነብበው፤ ከእስራኤል ወገን የሆኑ ሌሎች የጠፉ ነገዶች ወይም ዘሮች ያሉ ሊያስመስል ይችላል። ነገር ግን የትም ቦታ ኢየሱስ ከእስራኤል ለሆነ አንድ የጠፋ ነገደ ወዘተ ነው የተላኩት የሚል ነገር ተናግሮ አያውቅም፤ ይህንንም ሲያደርግ አይታይም። እንዲህ ያለ የተሳሳተ ሃሳብ፤ ማለትም ከእስራኤል ነገዶች ሁሉ አንዱን ነጥሎ ኢየሱስ የፈለገበት ወዘተ ነገር በወንጌላቱ አንድም ቦታ የለም። ብዙ ጊዜም ጥቅስን ብቻ ከአውዱ(context) መነጠል አደጋው እዚህ ላይ ነው። ጨርሶ absurd ወደሆነ መደምደሚያ እንድንደረስ ያደርገናል።

ነገር ግን ይህን ክፍል ጥቅሱን ብቻውን ነጥለን ሳይሆን ከጠቅላላው የወንጌላቱ ታሪክ ጋር ስንመለከተው ግልጽ የሚያደርገው፤ በሥጋው ወራት ኢየሱስ ክርስቶስ ከአብ የተላከበት ተልዕኮ 
(mission) ለአይሁዶች ብቻ እንጂ ለአሕዛብ እዳልሆነ የሚያሳይ ነው። ማለትም በሥጋ ኢየሱስ መጥቶ አዲሱን ኪዳን እንዲመሠረት የተላከው ለአይሁዶች ነው። ማቴዎስ 10 ላይ ብንመለከት ኢየሱስ ደቀመዛሙርቱን ሲልካቸው ወደ አይሁዶች ብቻ ነበር የላካቸው። ምክንያቱም ኢየሱስ በቅድሚያ ሕግን መፈጸምና በሕግ ያለነቀፋ ሆኖ መገኘት ነበረበት። በኤርምያስ 31፡31 ላይ እንደተጻፈውም አዲሱ ኪዳን መደረግ ያለበት ከእስራኤል ቤት ጋር ነው።

አይሁዳውያን የእግዚአብሔር ልጅ ራሱ መጥቶ ነው ወንጌልን የሰበከላቸው፤ ወደ አሕዛብ ደግሞ እንደ ጳውሎስ ያሉ ሐዋርያት ናቸው የተላኩት። ኢየሱስ ራሱ ወደ አሕዛብ ሁሉ እየሄደና ዓለምን እየዞረ ወንጌልን እንዲሰብክ ይህ ተልዕኮ አልተሰጠውም ነበር።

ስለዚህ ኢየሱስ በዚህ ክፍል የሚናገረው እስከሚሰቀል ድረስ በሥጋው እንደ እግዚአብሔር መልእክተኛ የተላከው ለአሕዛብ ወንጌልን ለመስበክ ሳይሆን ለአይሁድ እንደሆነ ነው። ለምሳሌ ጳውሎስ የእርሱን አገልግሎትና የኬፋን 
(የጴጥሮስን) አገልግሎት ሲያወዳደር፤ እርሱ ለአሕዛብ ጴጥሮስ ደግም ለአይሁድ እንደተላኩ ይገልጻል።
ወደ ገላትያ ሰዎች
2፥7 ተመልሰው ግን ጴጥሮስ ለተገረዙት የሆነው ወንጌል አደራ እንደ ተሰጠው እንዲሁ ለእኔ ላልተገረዙት የሆነው ወንጌል አደራ እንደ ተሰጠኝ አዩ፤
2፥8 ለተገረዙት ሐዋርያ እንዲሆን ለጴጥሮስ የሠራለት፥ ለእኔ ደግሞ ለአሕዛብ ሐዋርያ እንድሆን ሠርቶአልና።
2፥9 ደግሞ የተሰጠኝን ጸጋ አውቀው፥ አዕማድ መስለው የሚታዩ ያዕቆብና ኬፋ ዮሐንስም እኛ ወደ አሕዛብ እነርሱም ወደ ተገረዙት ይሄዱ ዘንድ ለእኔና ለበርናባስ ቀኝ እጃቸውን ሰጡን፤

ልክ እንደዚሁ የኢየሱስም የሥጋው ወራት አገልግሎት ለአይሁድ ብቻ የተወሰነ ነበር።

የጠፉት በጎች ሲል ደግሞ ስለ አንድ ነገድ ወዘተ ሳይሆን ከእግዚአብሔር ርቀው ስላሉ ኃጢአተኛ እስራኤላውያን እንደሚናገር የሚያሳዩ ክፍሎችን መመልከት ይረዳል።
የሉቃስ ወንጌል 5
30 ፈሪሳውያንና ጻፎቻቸውም በደቀ መዛሙርቱ ላይ። ስለ ምን ከቀራጮችና ከኃጢአተኞች ጋር ትበላላችሁ ትጠጡማላችሁ
? ብለው አንጐራጐሩ።
31 ኢየሱስም መልሶ፦ ሕመምተኞች እንጂ ባለ ጤናዎች ባለ መድኃኒት አያስፈልጋቸውም፤
32 ኃጢአተኞችን ወደ ንስሐ እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁም አላቸው።

በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 15 ያለውንም የጠፋውን ልጅ ታሪክ ስንመለከት፤ ሁለቱ ልጆች አንደኛው በቤት ያለው ሁለተኛው ደግሞ የጠፋው ልጅ ታሪክ የሚያወራው ስለ ነገዶች ሳይሆን በኃጢአት ስለወደቀና ከአባቱ ርቆ በኃጢአት ከጋለሞቶች ጋር ገንዘቡን ስለበተነ ኃጢአተኛ ልጅ ነው።

ስለዚህ ኢየሱስ ከእስራኤል ስለ ጠፉት ማለትም ከእግዚአብሔር ርቀው ኃጢአተኛ የሚባሉትን ሊፈልግ እንደመጣ ነው እንጂ የሚናገረው የሆነ የእስራኤል ነገድን ሊፈልግ አይደለም። በወንጌላቱ የተጻፉትን አገልግሎቱንም ስንመለከት ኢየሱስ ጋለሞታዎችን፤ ቀራጮችን፤ ኃጢአተኞችን ወዘተ ሲፈልግና እነርሱን ሲያገለግል ነው የምናየው
ወንድማቹ ሸዋፈራው አለነ
የጌታ ሰላም ከሁላችንም ጋር ይሁን

bX-h26akd

አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ›› (ማቴ 27፡46)/ይድረስ ለአህዛብ እና አርዮሳውን/
‹‹ልጁ እራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል››  1ኛ ቆሮ 15፡22 ምን ማለት ነው
   በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
  ውድ እህትና ወንድሞቼ እንደምን አላቹልኝ እንደእግዚአብሔር ፈቃድ ዚህን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል እውነተኛ ትርጉም እናያለን ብዙ ጊዜ እስላሞች  ራሳቸውን የይሖዋ ምስሮች በማለት የሚጠሩ አርዮሳውያን እና መናፍቃን ፕሮቴስታንቶች እና ያናገርኳቸው አንዳንድ ተሀድሶዎች ይህንን ጥቅስ በመያዝ ወልድ ሁሉን እንዲገዛ ስልጣንን የሰጠው አብ ነው ነገር ግን ወልድ ሁሉን ላስገዛለት ለአብ ይገዛል ስለዚህ ወልድ ከአብ ያነሰ ስልጣን ነው ያለው ይላሉ፡፡አህዛብ እና አርዮሳውያን ይህንን ቢሉም አይደንቀኝም ነገር ግን የኢየሱስን አምላክነት እናምናለን ሥላሴም እንታመናለን ብለው የሚናገሩ ፕሮቴስታንቶች ይህንን ማለታቸው በጣም የሚያሳዝን እና በአንደበት አምላክነቱን እናምናለን ቢሉም በተግባር እንደካዱት የሚያሳይ ነው፡፡
  ገፀ ንባቡን በማስተዋል ካነበብነው ቅዱስ ጳውሎስ እየተናገረ የመጣው ስለትንሳኤ ሙታን እና ክርስቶስ ሞትን ድል ስለማድረጉ ብሎም ሞት በሁሉም ላይ ስላለመሰልጠኑ ኃይሉንም ስለመሻሩ ነው እስኪ ከቁጥር 20 ጀምረን እንመልከተው ‹‹አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነስቷል ሞት በሰው በኩል ስለመታ ትንሳዔ ሙታን በሰው በኩል ሆኗል ሁሉም በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁም በክርስቶስ ህያዋን ይሆናሉና ነገር ግንእያንዳንዱ በራሱ ተራ ይሆናል ክርስቶስ እንደበኩራት ነው በኋላም በመምጣቱ ለክረስቶስ የሆኑት ናቸው በኋላም መንግስቱን ለአባቱ ለእግዚአብሔር አሳልፎ በሰጠ ጊዜ አለቅነትንም ስልጣንንም በሻረ ጊዜ ፍፃሜ ይሆናል ››አለቅነትንም ስልጣንንም በሻረ ጊዜ ፍፃሜ ይሆናል የሚለው የአለም ፍፃሜ የሚሆነው የዚህ አለም ገዢዎች እና አለቆች ስልጣናትን ኃይላትን ስልጣናቸው ተሽሮ መሆኑን ለማስረዳት ነው ምክንያቱም በሌላም ቦታ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ብሏል ‹‹መጋደላችን ከስጋና ከደም ጋር አይደለምና ከአለቆችና ከስልጣናት ከዚህም ከጨለማ አለም ገዥዎች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ባሉ ከክፋት መንፈሳዊ ሰራዊት ጋር ነው እንጂ››ኤፌ 6፡12 ቀጥሎ ደግሞ ከቁጥር 25-27እንዲህ ይላል ‹‹ጠላቶቹን ሁሉ ከእግሩ በታች እስኪያደርግ ድረስ ሊነግስ ይገባዋልና የኃለኛው ጠላት የሚሻረው ሞት ነው ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዝቷልና ነገር ግን ሁሉ ተገዝቷል ሲባል ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጥ ነው ››
‹‹ጠላቶቹን ሁሉ ከእግሩ በታች እስኪያደርግ ድረስ ሊነግስ ይገባዋልና ››የተባለው ለወልድ ነው ጠላቶች የተባሉትም ሞትና ዲያብሎስ ናቸው፡፡ዘፍ 3፡15 እንዲ ተብሏል ‹‹በአንተ እና በሴቲቱ በዘርና በዘርዋ መካከል ጠላትነትን አደርጋለው ››በምፅአት ቀን የሞትና የዲያብሎስ ስልጣን ያከትማል ‹‹ከእግሩ በታች እስኪያደርግ ድረስ ሊነግስ ይገባዋል ››ሲል ከገዛ በኋላ እንደምድራዊ ሹም ሥልጣኑን አስረክቦ ይወርዳል ለማለት ሳይሆን ለዘለአለም ንጉስ ሆኖ ይኖራል ማለት ነው እዚህ ላይ የገባችው ‹‹እስከ›› ፍፃሜ የለሽ ወይም ዘላለማዊ‹‹እስከ›› ነች ለምሳሌ ‹‹የሳኦል ልጅ ሜልኮል እስከሞተችበት ቀን ድረስ ልጅ አላወለደችም ››2ሳሙ6፡23ይህ ማለት ሜልኮል ከሞተች በኋላ ወልዳለች ለማለት ሳይሆን ለዘለአለም ሳትወልድ ቀረች ማለት ነው ዘፍ 8፡6‹‹ቁራውም ውሀው ከምድር ላይ እስኪደርቅ ድረስ ወዲያና ወዲህ ይል ነበር ››ይላል እዚህ ላይም ቁራው ውሀው ከጎደለ በኋላ ተመለሰ ለማለት ሳይሆን እስከመጨረሻው ሳይመለስ ቀረ ለማለት ነው ኖህ ቁራው ሳይመለስ ስለቀረ ነው እርግብን የላካት፡፡ አንድም ስልጣኑን ለአባቱ አሳልፎ በሰጠ ጊዜ የተባለው ጌታ በወንጌሉ ‹‹እረኛው አንድ መንጋውም አንድ››ዮሐ 10፡16 እንዳለ በመጨረሻው ዘመን የክርስቶስ መንግስት በስላሴ መንግስት ይጠቃለላል ማለትም ክርስቶስ ብቻ ይገዛ የነበረው የምድራዊ መንግስት/ሞቶ ስላዳነ ያዳናቸውን ሰዎች እየገዛ ያለው ክርስቶስ ስለሆነ/ያ የብቻው መንግስት በክርስቶስ ተጠቅልሎ የስላሴ መንግስት ይሆናል ማለቱ ነው ፡፡ክርስቶስ መንግስቱን ይተዋል ማለት ግን አላዋቂነት ነው ምክንያቱም በተለያየ ቦታ ለዘለአለም እንደሚገዛ ነው የተፃፈው ሉቃ 1፡33፤ዕብ1፡8
 ቀጥሎ ደግሞ ‹‹ሁሉ ተገዝቷል ሲል ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጥ ነው ›› ሁሉ የተባለው ከአዳም ጀምሮ ያለው የሰው ዘር ነው ሞት የሰው ዘርን በሙሉ ከትንሽ እስከትልቅ ፃድቃን እና ሀጥእ ሳይል ሁሉን ገዝቶ በሁሉም ላይ ሰልጥኖ ይኖር ነበር ነገር ግን ሞት ሁሉን ገዛ ቢባልም‹‹ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጥ ነው››ሁሉን ያስገዛለት የተባለው እግዚአብሔር ነው፡፡ሐዋርያው ይቀጥልና ቁጥር 28 ላይ ‹‹ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል››ይህም ማለት የእግዚአብሔር አብ አንድያ ልጁ ወልድ ሁሉን ላስገዛለት ለሞት እሱ ራሱ በስጋው ይገዛለታል ማለት ነው፡፡ሞት ወልድን ሳይቀር በስጋው ይገዛዋል ነው ምክንያቱም እንዲህ ተብሏል ‹‹የባርያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሁኖ ራሱን ባዶ አደረገ……ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳን የታዘዘ ሆነ››ፌል2፡7-8ወልድ ‹‹ለሞት ተገዛ ››ስንል በፈቃዱ ነው በእለተ አርብ በቀራንዮ ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ስጋው በገዛ ስልጣኑ መለየቱን ለማስረዳት ነው፡፡አስቀድሞ ጌታ እንዲህ ብሏል ‹፣ነፍሴን ደግሞ አነሳት ዘንድ አኖራታለውና›› ……እኔ በፍቃዴ አኖራታለው እንጂ ከእኔ ማንም አይወስዳትም ላኖራት ስልጣን አለኝ ላነሳት ስልጣን አለኝ፡፡ዮሐ10፡17-18 ስንጠቀልለው ልጁ ራሱ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል ማለት ለአብ ይገዛል ማለት ሳይሆን ከላይ እንዳየነው ሁሉን ላስገዛለት ሞት በፈቃዱ ይገዛል ይህም ተፈፅሟል የመፅሐፍ ልማድ የተደረገውን ገና እንደሚደረግ ያልተደረገውን እንደተደረገ አድርጎ ማውራት ልማድ ነው፡፡
ይቆየን
ወንድማቹ ሸዋፈራው አለነ
ወስብሀት ለእግዚአብሔር
 
 

ዓርብ 13 ማርች 2015

ኢየሱስ ያስታረቀን አማልዶ ወይንስ እዳችንን ከፍሎ?ሊቀካህን ተግባሩስ ምንድነው ማማለድ ወይንስ መስዋእት ማቅረብ?
ይህንን ፅሑፍ እንድፅፍ ያነሳሳኝ ነገር በዚህ በፌስ ቡክ ገፅ መናፍቃን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር የመጣበትን አላማ ባለመረዳት ኢየሱስ ክርስቶስ ክብር ይግባው እና አማላጅ ነው ብለው ሲፅፉ በመመልከቴ ነው ይባስ ብለውም አጫፋሪዎቻቸው የኛዎቹም ተሀድሶ ነን ባዮችብለው ብለው ይህንን ቃል ደጋግመው ሲናገሩ እንሰማለን እንዲህም ይሉናል ኢየሱስ ያማልዳል ማለታችን አሁን በአብ ዘንድ እየተነሳ እየወደቀ ያማልዳል ማለታችን ሳይሆን አንድ ጊዜ ያፈሰሰው ደሙ እና የቆረሰው ስጋ እየጮኸ ልመናን ያቀርባል ማለታችን ነው ብለው አሻሽለው አዲስ ዶክትሪን ቀርፀዋል፡፡ለመሆኑ ኢየሱስ የሞተው ሊያማልደን ነው ወይስ ሊያስታርቀን ደሙስ አማለደን ነው የምንለው እዳችንን ከፍሎ አስታረቀን መፅሐፍ ቅዱስን መሰረት አድርገን እንማማራለን ልብ ብላችሁ ፅሑፉን አንብቡ፡፡በመጀመሪያ ማማለድ ማለት በቀላል አማርኛ መለመን ማለት ነው ኢየሱስ አዳም በበደለው በደል የተፈረደበትን ፍርድ ያስወገደው በልመና ፀሎትን በመማቅረብ ሳይሆን እዳውን ከፍሎ በማስታረቅ ነው ማስታረቅ እና መማለድ የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡ከላይ እንዳልነው ማማለድ መለመን ነው ማስታረቅ ደግሞ አንተም ተው አንተም ተው ብሎ ማቀራረብ ወይም ማገናኘት አልያም አንድን ሰው ወክሎ ያሰው ያጠፋውን ጥፋት በደል መካሻ የሚሆን ካሳ ለተበዳዩ ወገን አቅርቦ ሁለቱን ወገኖች ባቀረበው ካሳ ማገናኘት ወይም ምህረትን ማድረግ ማለት ነው፡፡
መናፍቃኑ እንደሚሉት በአዳም ምክንያት የመጣብን በደል እና ሀጢያት በምልጃ በልመና የሚቀረፍ ወይም የሚወገድ አይደለም በልመና የሚወገድ ቢሆን ኑሮ ብዙ ቅዱሳን አባቶች በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔርን ለምነዋል ወደእርሱም ጩኀዋል ፅድቃችን እንደመርገም ጨርቅ ተቆጠረ በማለት ምሬትን አቅርበዋል ግን ይህ ሁሉ ጩኸታቸው ይህ ሁሉ ልመናቸው ፍፁም እርቅን ድህነትን ሊያመጣላቸው አልቻለም ከመርገም ሊያስወግዳቸው አልቻለም ምክንያቱም ንፁ የሆነ በደል የሌለበት ሰው ተበዳዩን አካል ለብሶ መከራን ተቀብሎ ካሳ መካስ ስለነበረበት ነው ታድያ መርገም በምልጃ በልመና የሚወገድ ቢሆን ኑሮ ቅዱሳኑ በልመና ከእግዚአብሄር ጋር መታረቅ በቻሉ ካህናቱም ህዝቡና ወደእግዚአብሔር ማቅረብ በቻሉ ነበር፡፡ምክንያቱም ያለደም ስርየት ስለሌለ የግድ የደም መስዋእት ያስፈልግ ነበር ካህናቱም ቢሆኑ በእግዚአብሄር ፍቃድ ምንም ሀጢያት የሌለባቸውን ነገር ግን ሰውን ሀጢያት ማስወገድ የማይችሉትን የእንስሳት ደም ያቀርቡ ነበር ግን ይህ መስዋእት ድህነትን ማምጣት አልቻለም ፡፡ፍፁም ድህነት የሚመጣው የበዳዩን የሰው አካል የለበሰ ፍፁም ንፁ የሆነ አካል ደም ሲፈስ ብቻ ነው ፡፡
ከላይ አንደተመለከትነው ኢየሱስ አማልዶ አስታረቀን ማለት ፍፁም ኢ-መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው ኢየሱስ እኛን ያስታረቀን እዳችንን ከፍሎ ፍፁም ራሱን ለሁሉ ቤዛ አድርጎ በመስጠት ነው፡፡ ይህም መፅሐፍ ቅዱሳዊ እውነት እንደሆነ እንመልከት ፡-
1.‹‹ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው››2ቆሮ 5፡18
ከዚ ጥቅስ እንደምንረዳው ቅዱስ ጳውሎስ እንደሚነግረን ከእግዚአብሔር ጋር ራሱ እግዚአብሄር ከስጋ ጋር ተዋህዶ ከራሱ ጋር እንዳስታረቀን ነው ስለዚህም አማልዶ ለምኖ ሳሆን እርቅ የፈፀመው ዋጋ ከፍሎ እንደሆነ መረዳት ያስፈልጋል፡፡
2.‹‹ ጠላቶች ሳለን ከእግዚአብሔር ጋር በልጁ ሞት ከታረቅን፥ ይልቁንም ከታረቅን በኋላ በሕይወቱ እንድናለን፤›› ሮሜ 5፡10
ይሄ ጥቅስ የተነሳንበትን ሀሳብ ይበልጥ ግልጽ ያደርገዋል ከእግዚአብሔር ጋር ማለትም ከአብ ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ታረቅነው በኢሱስ ሞት እንደሆነ እርቁም ተፈፀመው በልመና ሳይሆን ራሱን በማቅረብ እንደሆነ ልንገነዘብ ያስፈልጋል፡፡
3. ‹‹ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው።›› ኤፌ 2፡16
3. ‹‹እናንተንም ነውርና ነቀፋ የሌላችሁና ቅዱሳን አድርጎ በእርሱ ፊት ያቀርባችሁ ዘንድ፥ በፊት የተለያችሁትን ክፉ ሥራችሁንም በማድረግ በአሳባችሁ ጠላቶች የነበራችሁትን አሁን በሥጋው ሰውነት በሞቱ በኩል አስታረቃችሁ።›› ቆላ 1፡21;22
ክርስቶስ በሞቱ እንዳስታረቀን ልብ በሉ
4. ‹‹እግዚአብሔር ሙላቱ ሁሉ በእርሱ እንዲኖር፥ በእርሱም በኩል በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድር ወይም በሰማያት ያሉትን ሁሉ ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዶአልና።›› ቆላ 1፡19;20
5. ‹‹እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ።›› 2ቆሮ 5፡17
መፅሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን ክርስቶስ እኛን ከእግዚአብሔር /ከሶስቱ አካላት ጋር/ያስታረቀን አማልዶ ሳይሆን እዳችንን ከፍሎ እንደሆነ ቀጥለን እንመልከት፡፡
1. ‹‹እርሱም የክብሩ መንጸባረቅና የባሕርዩ ምሳሌ ሆኖ፥ ሁሉን በስልጣኑ ቃል እየደገፈ፥ ኃጢአታችንን በራሱ ካነጻ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ፤›› ዕብ 1፡3
ልብ በሉ ሀጢያታችንን አማልዶ አነፃ አይልም በስልጣኑ ሀጢያታችንን እንዳነፃ ነው የሚናገረው፡፡
2.‹‹ ይልቁንስ እንግዲህ አሁን በደሙ ከጸደቅን በእርሱ ከቍጣው እንድናለን።›› ሮሜ 5፡9
እንግዲህ ደሙ ይለምናል ማለት ምን ያክል ከመፅሐፍ ቅዱስ ጋር እየተቃረኑ እንደሆነ ተመልከቱ በደሙ እንድናለን እንፀድቃለን እንጂ የሚለው ደሙ ይማልድልናል አይልም
3. ‹‹ነገር ግን እርሱ በብርሃን እንዳለ በብርሃን ብንመላለስ ለእያንዳንዳችን ኅብረት አለን፥ የልጁም የኢየሱስ 
ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል።›› 1ዮሐ 1፡7
እንዴት ያሳርፋል ደሙ ሀጢያትን ያጥባል ተመልከቱ አሁንም ይማልዳል አይልም ደሙ የሰውን ሀጢያት ያጥብ ዘንድ ይቻለዋል፡፡
4.‹‹ ነውር የሌለው ሆኖ በዘላለም መንፈስ ራሱን ለእግዚአብሔር ያቀረበ የክርስቶስ ደም እንዴት ይልቅ ሕያውን እግዚአብሔርን ልታመልኩ ከሞተ ሥራ ሕሊናችሁን ያነጻ ይሆን?›› ዕብ 9፡14
የኛ ጌታ ደም ከሀጢያት ሁሉ የሚያነፃ ከእግዚአብሔር ጋር ያስታረቀን ወደእርሱ ያቀረበን ንጹ ደም ነው ማዳን የሚቻለው ደም ነው ታድያ ደሙ ማዳን ሀጢያታችንን ማጠብ እየቻለ ለምን ለምናል ለምንስ ያማልዳል፡፡
ሊቀካህን ተግባሩ ምንድን ነው?
በብሉይ ኪዳንም ሆነ በእብራውያን መልእክት እንደምናነበው የሊቀካህናት ተግባር የነበረው የእንስሳት መስዋእት ይዞ ቤተመቅደስ በመግባት መጀመሪያ ስለራሱ ሀጢያት በኋላም ስለህዝቡ ሀጢያት እግዚአብሔር ምህረት እንዲያደርግ መስዋእት ያቀርብ ነበር ፡፡ልብ በሉ የብሉይ ኪዳኑ ሊቀካህን መስዋእት በማቅረብ እንጂ ምልጃን በማቅረብ አይደለም ጊዜያዊ የህዝቡን ሀጢያት ያስተሰርይ የነበረው፡፡መስዋእት አቅራቢው ካህኑ መስዋእቱ የእንስሳት ደም መስዋእት ማቅረቢው ታቦቱ እና ለእርሱ ተዘጋጀ ቦታ መስዋእት ተቀባዩ እግዚአብሔር ነበር፡፡ስለዚህም የሊቀካህናት ተግባሩ መስዋእት ይዞ ወደእግዚአብሔር በመቅረብ የህዝቡን ሀጢያት በማስወገድ እንጂ ምልጃ በመያዝ አይደለም፡፡
ኢየሱስም የሀዲስ ኪዳን ዘላለማዊ ሊቀካህናት ሲባል ከብሉይ ኪዳኑ ሊቀካህናት የተሻለ ሊቀካህን ስለራሱ ሀጢያት መስዋእት ማቅረብ የማያስፈልገው ንፁህ ሊቀካህን ዘላለማዊ መስዋእት አንድ ጊዜ ያቀረበ ሊቀካህን ፡፡መስዋእት አቅራቢ ሊቀካህን መስዋእት ተቀባይ ሊቀካህን ራሱን መስዋእት አድርጎ ያቀረበ ሊቀካህን ማለት ነው ያስታረቀንም ዘላለማዊ ሊቀካህንነቱማ ካቀረበው ዘላለማዊ መስዋእት ጋር የተያያዘ እንጂ የሚለምን ምህረት ሚያሰጥ ሊቀካህን ሁኖ አይደለም ፡፡ያም ለዘለአለም ያቀረበውን መስዋእት እስካለም ፍጻሜ እያመኑበት የሚመጡ ሰዎች ሲታረቁበት ይኖራሉ ማለት ነው ፡፡
1.‹‹ስለዚህ የሕዝብን ኃጢአት ለማስተስረይ፥ ለእግዚአብሔር በሆነው ነገር ሁሉ የሚምርና የታመነ ሊቀ ካህናት እንዲሆን፥ በነገር ሁሉ ወንድሞቹን ሊመስል ተገባው።›› ዕብ 2፡17 
የኛ ሊቀካህን ማህሪ ሊቀካህን ነው የኛ ሊቀካህን አቤቱታ አቅራቢ ሳይሆን አቤቱታ ተቀባይ ሊቀካህን ነው መሀሪ ይቅር ባይ ነው፡፡
2. ‹‹ከተፈጸመም በኋላ በእግዚአብሔር እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ሊቀ ካህናት ተብሎ ስለ ተጠራ፥ ለሚታዘዙለት ሁሉ የዘላለም መዳን ምክንያት ሆነላቸው።›› ዕብ 5፡9 
የኛ ሊቀካህን መዳናችንን የሰጠን ሊቀካህን ነው
3.‹‹ ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል››።ዕብ 7፡23-25
የኛ ሊቀካህን አዳኝ ሊቀካህን ነው የኛ ሊቀካህን መሀሪ ሊቀካህን ነው፡፡
አንድ ጊዜ ባፈሰሰው ደሙ ለዘላለም ስንታረቅበት/በስጋውና ደሙ /እንኖራለን ይህ ማለት ምልጃ ማለት አይደለም ያመኑ አዲስ ሰዎች ይታረቁበታል አንድ ጊዜ በአብ ፊት በስጋውና በደሙ በታየው መታየት እንድናለን ማለት ነው፡፡
ወደ ዕብራውያን
7፥27 
እርሱም እንደነዚያ ሊቃነ ካህናት አስቀድሞ ስለ ራሱ ኃጢአት በኋላም ስለ ሕዝቡ ኃጢአት ዕለት ዕለት መሥዋዕትን ሊያቀርብ አያስፈልገውም፤ ራሱን ባቀረበ ጊዜ ይህን አንድ ጊዜ ፈጽሞ አድርጎአልና።
9፥12 
የዘላለምን ቤዛነት አግኝቶ አንድ ጊዜ ፈጽሞ ወደ ቅድስት በገዛ ደሙ ገባ እንጂ በፍየሎችና በጥጆች ደም አይደለም። 
9፥26 
እንዲህ ቢሆንስ፥ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ብዙ ጊዜ መከራ ሊቀበል ባስፈለገው ነበር፤ አሁን ግን በዓለም ፍጻሜ ራሱን በመሠዋት ኃጢአትን ሊሽር አንድ ጊዜ ተገልጦአል። 
9፥27 
ለሰዎችም አንድ ጊዜ መሞት ከእርሱ በኋላም ፍርድ እንደ ተመደበባቸው፥ 
9፥28 
እንዲሁ ክርስቶስ ደግሞ፥ የብዙዎችን ኃጢአት ሊሸከም አንድ ጊዜ ከተሰዋ በኋላ፥ ያድናቸው ዘንድ ለሚጠባበቁት ሁለተኛ ጊዜ ያለ ኃጢአት ይታይላቸዋል።
10፥10 
በዚህም ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ አንድ ጊዜ ፈጽሞ በማቅረብ ተቀድሰናል። 
10፥14 
አንድ ጊዜ በማቅረብ የሚቀደሱትን የዘላለም ፍጹማን አድርጎአቸዋልና።
ስናጠቃልለው ጌታ ኢየሱስ ያስታረቀን አማልዶ ሳይሆን እዳችንን ከፍሎ ነው ሊቀካህናት መባሉም ዘላለማዊ መስዋእት በማቅረቡ ነው፡፡ በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለምልጃ የተጠቀሱት ክፍሎች ኢየሱስ ሰው እንደመሆኑ ስጋ እንደለበሰ ለማጠየቅ እና ፀሎትን ለማስተማር ያቀረበው ልመና ነው ፡፡የአብ ሊቀካህናት ጌታችን ሆይ ማረን ይቅር በለን ራራልን፡፡
የአብፀጋ የወልድ ቸርነት የመንፈስቅዱስ ህብረት ከሁላችንም ጋር ይሁን አሜን
ወንድማቹ ሸዋፈራው አለነ





 አፅናኙ ማነው?/ይድረስ ለመሀመዳውያን/
መቼም ብዙ ጊዜ በዚ በፌስ ቡክ የማናነበው የለም ሁሉም አማኙም መናፍቁም አህዛቡም የመፅሐፍ ቅዱስ ተርጓሚ እኔ ነኝ ይህ ማለት ይህ ነው እያለ የራሱን ትርጉም መስጠት ተያይዞታል፡፡በዚህ ለምን አልሰለምኩም በሚለው ፔጅ ውስጥ አን ወዳጅ ሙስሊም አለኝ እሱም በመፅሐፍ ቅዱስ ላይ የራሱን የሆነ ትርጉም አስቀምጧል እስቲ አብረን እንመልከተው፡-
<<@ኢየሱስ (አ.ሰ) በመፅሀፍ ቅዱስ ለነብያችን ሙሀመድ (ሰ.አ.ወ) መምጣት ብስራት (ትንቢት) ሲናገሩ፦ ገና የምነግራችሁ ብዙ አለኝ ። ነገር ግን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም። ግን እሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችሃል፤የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤የሚመጣውንም ይነግራችሃል። እሱ ያከብረኛል።ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችሃልና። ፼፼፼፼ እውነትም ነብያችን (ሰ.አ.ወ)ከራሳቸው ሳይሆን ከአላሀ (ሱ.ወ) የሚነገራቸውን ብቻ ይናገራሉ። እየሱስንም ያከብራል። ስለ እየሱስ አላሀ የነገረውን ሁሉ ተናግራል። አለምንም ወደቀጥተኛው የኢብራሂም መንገድ (ወደ ኢስላም) መርታል። አላሁ አክበር››
በመጀመሪያ አንድ ነገር ላስታውሳችሁ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለመጨረሻው ዘመን ሲናገር ወንጌል ለአህዛብ ምስክር ይሆን ዘንድ በአለም ሁሉ ይሰበካል ያለው ቃል እየተፈፀመ መሆኑን አሁን ያለነው ፍፃሜ ዘመን ላይ እንዳለን ነው ማቴ 24፡14
ከላይ እንዳየነው ሙስሊሙ ወዳጃችን /የሌሎቹም ሙስሊሞች አመለካከት ነው /ጌታኢየሱስ አፅናኙ መንፈስ ይመጣል ያለው መሀመድን ነው ብሏል፡፡ እስቲ አንድ ነገር ልንገርህ ወዳጄ ይህንን የጌታን ቃል ለመሀመድ ሰጥተክ ከተናገርክ ሌላውንም የወንጌል ቃል ማመን እንዳለብህ ማወቅ አለብህ አንዱን ቃል ብቻ መዞ ማመን አይቻልም ጌታ ስለሀጥያታችን መሞቱን መሰቀሉን መነሳቱን ሰው መሆኑን አዳኝ ጌታ አምላክ መሆኑን ማመን አለብህ ምክንያቱም በወንጌል ተመዝግቦ ያለውን የጌታ ቃል ለመሀመድ እንደተነገረ በማመንህ የወንጌልን እውነተኛነት ተቀብለሀል ማለት ነው ይህንን ስል ትንቢቱ ለመሀመድ ተነገረ እያልኩኝ አይደለም፡፡
ትንቢቱ የተነገረው ይመጣል የተባለው አፅናኝ መሀመድ ነው ካላችሁ እነዚህን ጥያቄዎች መልሱ
1.ጌታ መንፈስ እንደሚመጣ ነው የተናገረው መሀመድ መንፈስ ነው እንዴ? ስጋና አጥንት የለውም? ሰውስ አይደለም እንዴ? ይህንን እንድትመልሱልኝ እፈልጋለሁ፡፡ ምክንያቱም ጌታ ይመጣል ያለው አፅናኙ መንፈስ እንጂ ስጋና አጥንት ያለው ሰው ነው አላለም፡፡
2.ለመሆኑ መሀመድ ኢየሱስን አክብሯል እንዴ? ምክንያቱም ኢየሱስ የያከብረኛል ስላለ
3.ኢየሱስ ከእኔ ወስዶ ይነግራችኋል ብሏል መሀመድ ከኢየሱስ ወስዶ እንደተናገረ ታምናላችሁ?
በተረፈ የጥቅሱን ሀሳብ ፍሬ ነገር በዝርዝር ቀጥሎ እንመልከት፡-

‹ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ
ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤
እርሱም ዓለም የማያየውና የማያውቀው ስለ ሆነ ሊቀበለው
የማይቻለው የእውነት መንፈስ ነው፤ ነገር ግን ከእናንተ ዘንድ
ስለሚኖር በውሥጣችሁም ስለሚሆን እናንተ ታውቃላችሁ።
ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ
እመጣለሁ። ዮሐንስ 14.15-18፡፡ ‹ከእናንተ ዘንድ ስኖር ይህን
ነግሬአችኋለሁ፤ አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ
የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም
የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል። ዮሐንስ 14.25-26፡፡ ‹ዳሩ
ግን እኔ ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ አጽናኝ እርሱም ከአብ
የሚወጣ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ፥ እርሱ ስለ እኔ
ይመሰክራል፤ እናንተም ደግሞ ከመጀመሪያ ከእኔ ጋር
ኖራችኋልና ትመሰክራላችሁ። ዮሐንስ 15.26-27፡፡
በሚገርም ሁኔታ ሙስሊሞች እነዚህን ጥቅሶች የሚያዩአቸው
ስለ መሐመድ መምጣት ትንቢቶች እንደሆኑ አድርገው ነው፡፡
በእርግጥ ስለ አፅናኝ የተነገረባቸውን እነዚህን ሦስት ጥቅሶች
በሙሉ ከጠቀሰ በኋላ፣ ሙላና መሐመድ አሊ የያዘው ‹ሁሉም
እነዚህ የትንቢት ቃሎች ያለምንም መዛነፍ የሚናገሩት ነገር
ከኢየሱስ በኋላ ስለሚመጣ ሌላ ነቢይ ነው›፡፡ የሚልን አቋም
ነው፡፡ Maulana Muhammad Ali, Muhammad in the
Bible, p. 27.
‹ኢየሱስ ወደ አባት ካልተመለሰ በስተቀር አፅናኙ አይመጣም›
የሚለው ይህ ትንቢት ስለ መንፈስ ቅዱስ በፍፁም ሊናገር
አይችልም በማለት ሙስሊሞች ይከራከራሉ፡፡ ምክንያቱም
መንፈስ ቅዱስ በራሱ በኢየሱስ ውስጥ ስለነበረ ነው ይላሉ፡፡
ስለዚህም ኢየሱስ ይናገር የነበረው ስለ ሌላ ነቢይ መነሳት
ወይንም መምጣት ነበረ፣ ስለዚህም (ለተወሰኑ ምክንያቶች)
ተመራጭ ሊሆን የሚችለው ነቢይ መሐመድ ብቻ ነው፡፡
እንደዚህ ዓይነት አባባል ደግሞ የዮሐንስ ወንጌልን ለሚያውቅ
ሰው እጅግ አስገራሚ ነው የሚሆነው፡፡
በመጀመሪያ ሙስሊሞች ይህንን ትንቢት ወሰድን የሚሉት
ከመጀመሪያው ጀምሮ ኢየሱስ አምላክ መሆኑን እና ሁሉን ነገር
የፈጠረ ነው ከሚለው መጽሐፍ ማለትም ከዮሐንስ 1.1-3 ላይ
ነው፡፡ በዮሐንስ መጽሐፍ ኢየሱስ የተናገረው ከአብርሐም በፊት
እርሱ እንደነበረ ነው 8.58፡፡ እንዲሁም እራሱን በሰማይና
በምድር መካከል እንዳለ መሰላል አድርጎ ነው 1.51 ይህም
በዘፍጥረት 28.10-17 ላይ እንዳለው ነው፡፡ ከዕውርነቱ
የተፈወሰው እና ማየትን የተሰጠው ሰው ኢየሱስን አምልኮታል፣
እንዲሁም ቶማስ ኢየሱስን ‹አምላኬና ጌታዬም› ብሎ 20.28
ላይ ጠርቶታል፡፡ ጌታ ኢየሱስ በዚህ ወንጌል ዘገባ ውስጥ
ተሰቅሏል፣ ሞቷል፣ እና ደግሞም ተነስቷል፣ እነዚህም ሁሉ
ለቁርአን እጅግ ልዩ የሆኑ ወይንም ተቀባይነት የሌላቸው
ነገሮች ናቸው፡፡ ከዚህም በላይ በዚያው በተመሳሳይ ምዕራፍ
ውስጥ ሙስሊሞች ስለመሐመድ ትንቢት አለበት በማለት
በሚጠቅሱት ውስጥ ኢየሱስ እርሱ ብቻ ወደ እግዚአብሔር
የሚወስድ መንገድ እንደሆነ ተናግሯል 14.6፣ እርሱን ያየ
ማንም ቢኖር አብን እንዳየ ተናግሯል፣ 14.9. እርሱ በአብ
ውስጥ አብ ደግሞ በእርሱ ውስጥ እንደሆነም ተናግሯል፣
14.11፣ እርሱ ፀሎትን እንደሚመልስ ተናግሯል፣ 14.14፡፡
እኛም በእርሱ ውስጥ የማንኖር ከሆነ ምንም ፍሬ ሊኖረን
እንደማይችልም ተናግሯል፣ 15.4፡፡ እኛ እንደዚህ እስልምናን
በጣም የሚቃወምን መጽሐፍ ሙስሊሞች ለመጥቀሳቸው
በጣም እንደነቅ ይሆናል፣ ይሁን እንጂ ማስታወስ ያለብን ነገር
መሐመድ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ስለ እርሱ የተነገሩ ትንቢቶች
መኖራቸውን ስለመናገሩ መዘንጋት የለብንም፡፡ ስለዚህም
ሙስሊሞች የተገደዱት የመሐመድን ትንቢት ወይንም ንግግር
ሊደግፍላቸው ወይንም ሊያረጋግጥላቸው ይችላል ተብሎ
የሚታሰበውን ማንኛውንም ነገር ሁሉ ለመጨበጥ
መገደዳቸውን ነው፡፡
ሁለተኛ፡- በዮሐንስ ውስጥ ያሉት ሦስቱ ክፍሎች አፅናኙን
የሚገልፁት መንፈስ ቅዱስ ነው በማለት ለይተው ነው፣
(ወይንም የእውነት መንፈስ) በማለት ነው፡፡ ነገር ግን
ሙስሊሞች የሚከራከሩት እነዚህ ጥቅሶች ስለ መንፈስ ቅዱስ
በምንም ዓይነት አይናገሩም በማለት ነው፡፡
እነሱ እንደሚሉት የትንቢቱ ቃሎች ለመንፈስ ቅዱስ ነው
የሚያገለግሉት በማለት ወደ ድምዳሜ እንድምመጣ
አያስችሉንም፡፡ ይሁን እንጂ ‹እኔ ባልሄድ አፅናኙ ወደ እናንተ
አይመጣም› የሚሉት ቃላት ምንም መግለጫ የማያስፈልጋቸው
በጣም ግልጥ የሆኑ ናቸው፡፡ አዲስ ኪዳን የሚለው መጥምቁ
ዮሐንስ ገና ከመወለዱም በፊት በመንፈስ ቅዱስ እንደተሞላ
ነው፡፡ ከዚያም ስለ ኢየሱስ ሲናገር እርሱ መንፈስ ቅዱስን
በእርግብ መልክ እንደተቀበለ ነው፡፡ ስለዚህም መንፈስ ቅዱስ
ከኢየሱስ ጊዜ በፊትና በኢየሱስ ጊዜ ሰዎችን ይጎበኝ እንደነበረ
ነው፡፡ በመሆኑም የሙስሊሞች ክርክር ኢየሱስ የተናገረውን
ትንቢት ነጥብ ሙሉ ለሙሉ በግልፅ ስቶታል፡፡ ኢየሱስ መንፈስ
በእነሱ ውስጥ እንደነበረ ያውቃል ... በእናንተ ይኖራልና፡፡
ትንቢቱ ግን መንፈስ በእነሱ ይኖራል ከእነሱም ጋር ለዘላለም
ይኖራል ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሙሉ፤ ለሙሉ አዲስ ነገር ነው፡፡
እናም መንፈስ ቅዱስ በኢየሱስ ውስጥ ስለነበረ ሊሆን
አይችልም፣ ትክክልም አይደለም ተብሎ ሊነገር አይቻልም፡፡
ሦስተኛ፡- ከላይ እንዳየነው ሁሉ ጌታ ኢየሱስ የተናገረው
አፅናኙ ከደቀመዛምርቱ ጋር ለዘላለም እንደሚሆን ነው፡፡
ስለዚህም መሐመድ ለዘላለም ከእነሱ ጋር መሆንን ቀርቶ
ከኢየሱስ ደቀመዛምርት ጋር ሊሆን በምንም ዓይነት መንገድ
አይችልም ነበር፡፡
አራተኛ፡- በትንቢቱ መሰረት ዓለም አፅናኙን ሊቀበለው
አይቻለውም፣ ምክንያቱም ሊያየው አይቻለውምና፡፡ እጅግ ብዙ
ሺ ሰዎች መሐመድን በሕይወት በነበረበት ጊዜ አይተውታል
እርሱ ይታይ ነበርና፡፡ ስለዚህም የማይታየው አፅናኝ የሚታየው
መሐመድ ሊሆን አይችልም፡፡
አምስተኛ፡- ኢየሱስ ለደቀመዛምርቱ የነገራቸው አፅናኙ አራሱ
ከእነሱ ጋር እንደነበረ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከኢየሱስ
ደቀመዛምርት ጋር የነበረ ሲሆን መሐመድ ግን ከአምስት መቶ
ዓመታት በፊት ይህ ትንቢት ከተነገረ በኋላ ነበር የነበረው
ስለዚህም ከእነሱ ጋር እርሱ ሊኖር አይችልም ነበር፡፡
ስድስተኛ፡- አፅናኙ በደቀመዛምርቱ ውስጥ መሆን ነበረበት፡፡
መሐመድ በኢየሱስ ደቀመዛምርት ውስጥ አልነበረም
እንዲሁም ሊሆንም አይችልም፡፡ መንፈስ ቅዱስ በሌላ ጎኑ
ደግሞ አማኞችን በጴንጤ ቆስጤ ቀን ሞላባቸው ከዚያን ጊዜ
ጀምሮም በክርስትያኖች ሁሉ ውስጥ ይገኛል፡፡
ሰባተኛ፡- ኢየሱስ የተናገረው እርሱ አፅናኙን ከአብ ዘንድ
እንደሚልከው ነው፡፡ ሙስሊሞች መሐመድ በኢየሱስ እንደተላከ
አያምኑም እነሱም የሚያምኑት መሐመድ በእግዚአብሔር
እንደተላከ ነበር፡፡ ስለዚህም ሙስሊሞች ኢየሱስ እግዚአብሔር
ነው በማለት ካላመኑ በስተቀር ይህ ስለ መሐመድ የተነገረ
ትንቢት ነው በማለት ሊቀበሉት አይገባቸውም፡፡
በመጨረሻም፡- ከእርገቱ በፊት ኢየሱስ ተከታዮቹ ከጥቂት
ቀናት በኋላ በመንፈስ ቅዱስ እንደሚሞሉ ትንቢትን ተናግሮ ነበር
ሐዋርያት 1.5፡፡ ወደ አባቱም ከአረገ ከጥቂት ቀናት በኋላ
መንፈስ ቅዱስ በኢየሱስ ተከታዮች ላይ መጣ፡፡ ‹በዓለ ኀምሳ
የተባለውም ቀን በደረሰ ጊዜ፥ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው
አብረው ሳሉ፥ ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ
ድምፅ መጣ፥ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው።
እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም
ላይ ተቀመጡባቸው። በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥
መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው በሌላ ልሳኖች ይናገሩ
ጀመር።› ሐዋርያት 2.1-4፡፡
ስለዚህም የዚህ ትንቢት ፍፃሜ የሆነው በጥቂት ቀናት ውስጥ
ነበር፡፡ መሐመድ ግን የመጣው ከአምስት መቶ ዓመታት በኋላ
ነበር፡፡ እነዚህን ነገሮች ሁሉ በአንድ ላይ በማስቀመጥ
መሐመድ አፅናኙ ሊሆን እንደማይችል እንመለከታለን፡፡ እርሱ
ከደቀመዛምርቱ ጋር አልነበረም፣ እርሱ በሐዋርያቱ ውስጥ
አልነበረም፣ እርሱ ከእነርሱ ጋር ለዘላለም አልነበረም፣ እርሱ
የማይታይ አልነበረም፣ እርሱ በኢየሱስ አልተላከም ነበር እርሱ
(መሐመድ) ጌታ ኢየሱስ እንደተናገረው ከተተነበየ በኋላ
ወዲያውኑ አልመጣም ነበር፡፡ እነዚህ ሁሉ እውነታዎች
የሚያሳዩት በጌታ ከተተነበየው ትንቢት ጋር ሙሉ ለሙሉ
የሚገጥመው መንፈስ ቅዱስ ብቻ መሆኑን ነው፡፡ ኢየሱስ
አፅናኙን ለይቶ የተናገረው መንፈስ ቅዱስ ነው በማለት ነው፡፡
እርሱም ከደቀመዛምርቱ ጋር ነበር፣ በጴንጤቆስጤም እለት
በእነሱ ውስጥ ነበር እርሱ የማይታይ ነበር፣ የመጣውም
በፍጥነት ነበር፡፡ መንፈስ ቅዱስ በጌታ በኢየሱስ ነበር
የተላከው፡፡ እንዲሁም ከክርስትያኖች ጋር ለሁለት ሺ ዓመታት
አብሮ ነው ያለው፡፡ እነዚህን ነጥቦች ሁሉ ስንመለከት
ሙስሊሞች እነዚህ ጥቅሶች ለመሐመድ ነው የሚያመለክቱት
በማለት መናገራቸው በእርግጥ እራሳቸውን የሚያሳፍራቸው
ነገር መሆን ይኖርበታል፡፡









































ሐሙስ 12 ማርች 2015

ኢየሱስ አሁን አማላጅ ነው ወይ?
ከይስሀቅ አበባየሁ
ፍጥረታትን ከመፍጠሩ በፊት አስቀድሞ በዘላለማዊ ፍቅር በምልዓት የሚኖር እግዚአብሔር ይህንኑ ተቀድቶ የማይደርቅ ተወስዶ የማልቅ አምላካዊ ፍቅር ተጋርተው በእሱ ፍቅር ፀንተው የሚኖሩ ፍጥረታትን ለመፍጠር ወሰነ፡፡ ፍጥረታት የእግዚአብሔር ፍቃድ መገለጫ ናቸውና ፡፡ በመሆኑም ከብዙ ፍቅሩ ከምልዓት ፍቅሩ የተነሳ የምናየውንና የማናየውን ዓለም እግዚአብሔር ፈጠረ፡፡ ከነዚህ ፍጥረት እጅግ በረቀቀ አምላካዊ ግብር በራሱ ሃምሳልና አርዓያ የሰውን ልጅ ፈጠረ፡፡ የሰውን ልጅ ፈጥሮ በልጅነት አክብሮ ከሰማይ በታች ከምድርም በላይ ያለውን ፍጥረት ሁሉ በፀጋ አብዝቶ ለመንግስቱ ተካፋይ አደረገው፡፡ በመልኩና በአርያው የፈጠረውን ሰውን በምድር ሁሉ ላይ ያሉትን ፍጥረታት እንዲዛ ስልጣን ሰጠው፡፡ ነገር ግን ሁሉን ግዛ አስተዳድር ተብሎ የተሾመ አዳም የፈጣሪነት ስሜት እንዳይሰማው የተገዝነት ምልክት ይሆነው ዘንድ መልካሙና ክፉውን ከምታሳውቀው ከዚች ዘፍ አትብላ ብሎ ትዕዛዝ ሰጠው፡፡ የ አዳም ውድቀት አዳም ግን ፈጣሪው የሰጠውን የፀጋ (ስጦታ) ገዚነት አንሶት የባህሪይ አማላክ ሆኖ ለሰማይ ለምድርም ገዚ መሆን ተመኝቶ ዕፀበለስን በመብላቱ ፍጹም ቅጣት ተቀጣ፡፡ ከቦታው ተሰደደ ከማዕረጉ ተዋረደ ሞተ ስጋ ሞተ ነፍስ ለዲያቢሎሰ መገዛትን ያህል ከባድ ቀንበር ተጫነበት፡፡ (ዘፍ1÷2÷3) የአዳም ፀፀትና የእግዚአብሔር ፍርድ ከዚህ በኋላ ባደረገው ስህተት ተፀፅቶ በንስሐ ቢያለቅስ ቢጨነቅ ቢነሳ ቢወድቅ ከዲያቢሎስ ቁራኝነት መቼም ሊላቀቅ አልቻለም፡፡ በስህተቱ ፈፃሚዎች አዳምና ሔዋን ይቅርና ከነሱ የተወለዱ ሁሉ የነሱን መርገም ፍዳ የዘር የሚተላለፈው የዲያቢሎስ ተገዝነት በሁሉ ላይ ሆነ(ሮሜ 5÷12) በሰዋው መስዋዕት በፀለየው ፀሎት ባጠኑት ዕጣን ባቀረቡት ቁርባን(ስጦታ) ከዲያቢሎስ ተገዝነት ነፃ ሊዎጡ አልቻሉም፡፡ስለዚህ ነው ኢሳይያስ "ሰማዮችን ቀድደህ ምነው ብትወርድ! … ሁላችን እንደ ርኩስ ሰው ሆነናል፥ ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው"፡፡(ትንቢተ ኢሳይያስ 64÷1-12 ) አነዳዊት በተራቸው "እጅህን ከአርያም ላክ አድነኝም"(መዝሙረ ዳዊት 144÷7) ነብያቱ በአንድ ድምፅ ሆነው ወደ እግዚአብሔር አመለከቱ እንዲህ ያለ አገዛዝም ስለፀናባቸው በሥራቸው መፅደቅ ስለተሳናቸው በዚያን ጊዜ “ ከዲያቢሎስ የባርነት ፃህረኝነት ነፃ የሚያወጣን እርሱ ራሱ ሰው ሆኖ ነው እንጂ ሌላ አማላጅ አስነስቶ ወይም መልአክ ልኮ አይደለም እያሉ ክሶ ማስታረቅ ለክርስቶስ ብቻ የተመደበ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እኛም እንደዚሁ በክርስቶስ ካሳ መዳናችንን አውቀን አምነናል፡፡ በምድር ላይ ጻድቅ መታጣቱ መፃሕፍት ግን ከነአካቴውም “ሕያው ሁሉ በፊትህ ጻድቅ አይደለምና” (መዝ.143:2) ፤ “በዚህም አለም መልካም የሚሰራ ፃድቅ ኅጢአትም የማይሰራ ሰው የለም” (መክ 7፡20) ፤ “ፅድቃችን ሁሉ እንደመርገም ጨርቅ ተቆጠረ” (ኢሳ 63፡6) ፤ “ከርኩስ ነገር ንጹሕን ሊያወጣ ማን ይችላል? አንድ እንኳ የሚችል የለም” (ኢዮ.14:4) እያሉ አስተካክለው ይነግሩናል፡፡ ስለዚህም ሰው ሁሉ በታመነው በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ይፀድቃል እንጂ ከራሱ በምግባሩ ወይንም ከማናቸውም ፍጡር ፃድቅ እንደማያገኝ ኢዮብ ሲያስረዳ “ንጹሕ ይሆን ዘንድ ሰው ምንድር ነው? ጻድቅስ ይሆን ዘንድ ከሴት የተወለደ ምንድር ነው?”(ኢዮ.15:14) ይላል ፤ ቅዱስ ዳዊትም “በሥራቸው ረከሱ፥ ጐስቈሉ፤ በጎ ነገርን የሚሠራ የለም። የሚያስተውል እግዚአብሔርንም የሚፈልግ እንዳለ ያይ ዘንድ፤ እግዚአብሔር ከሰማይ የሰው ልጆችን ተመለከተ። ሁሉ ዐመፁ በአንድነትም ረከሱ በጎ ነገርን የሚሠራ የለም፤ አንድም ስንኳ የለም።” (መዝ.14:1-3) ጌታችን ኢየሱስ ሰውን ለማዳን በምድር ላይ መመላለሱ እንዲሁም አማላጅነቱ ዓለም ሁሉ በሠዋው መሥዋእት በፀለየው ፀሎት መዳን እንደተሳነው በሁሉ ዘንድ ከታወቀ ከተረዳ በኅላ አካላዊ ቃል ከቅድስት ድንግል ማርያም በድንግልና ያለወንድ ዘር ተፀነሰ ፡ ዲያቢሎስ በዘር ምክንያት በማህፀን ይቆራኝ ነበረ ፡ ቁራኝነት ቀረ ካሳ በማህፀን ተጀመረ፡፡ ሰው ሆነ ስጋ ለበሰ በዚህ ጊዜ በመንፀፈ ደይን ወድቆ አጋንንት ይጠቀጥቁት የነበረ የአዳም ባህርይ ከወደቀበት ተነሳ ከድካሙ ተፅናና በተዋህዶተ ቃል የባሕርይ አምላክ ሆነ ፡ በየማነ አብ በዘባነ ኪሩብ ተቀመጠ፡፡ ተወልዶም 30 ዘመን ሲሞላው በዮሃንስ እጅ ሲጠመቅ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጥሎ የነበረውን አዳም የእዳ ደብዳቤ ደመሰሰልን፡፡ አምላክ ሰው የሆነበት ፍሬ ነገሩ ዲያቢሎስ በወረወራቸው በሶስት ጦሮች በስስት በትእቢት በፍቅረ ነዋይ ተወግቶ ወድቆ ለነበረ ለአዳም ባህርይ ሃይል ለመስጠት ስለሆነ ስራውን በፆም ጀመረ፡፡ መፆሙም በሰውነቱ ነው እንጂ በአምላክነቱ አይደለም፡፡ ክርስቶስም በስስት የመጣበትን በትሕርምት ፡ በትእቢት የመጣበትን በትሕትና በፍቅረ ነዋይ የመጣበትን ንዋይን በመጥላት ግንባር ግንባሩን ብሎ ድል ከነሳው በኅላ መላእክት ሊያገለግሉት መጡ ፤ መላእክት ወደሱ መምጣታቸውም ድል ብትነሱ እንዲሁ መላእክት ወደእናንተም ይመጡላችኅል ሲለን እንደሆነ እናስተውል፡፡ ከዚህ በኅላ ምድረ እስራኤል ገብቶ ትምህርት ተአምራት ጀመረ ፤ መንግስተ ሰማያት በልጅነት ልትሰጥ ቀርባለችና ንስሐ ግቡ ብሎ አዋጅ ነገር፡፡ኑ ተከተሉኝ እኔ ድል እንደነሳሁ እናንተም ድል ንሱ ብሎ አስተማረ፡፡ ላመኑበትም በመንፈስ ቅዱስ ከእግዚአብሄር ተወልደው የእግዚአብሄር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣን ሰጣቸው፡፡ (ዮሐ 1÷11) 12ቱን ሃዋርያት ፡ 70 አርድእት መርጦ መንግስተ ሰማያት በልጅነት ልትሰጥ ቀርባለችና ንስሐ ግቡ እያላችሁ አስተምሩ ድውያንን ፈውሱ ፡ እናንተን የሰማ እኔን መስማቱ ነው ፡ እኔንም የሰማ የላከኝ አብን መስማቱ ነው ፡ እናንተን እምቢ ያለ እኔን እምቢ ማለቱ ነው ፡ እኔንም እምቢ ያለ የላከኝ አብን እምቢ ማለቱ ነው ብሎ ሾማቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም እነሆ አቤቱ ሁሉን ትተን ተከተልንህ እንግዲህ እኛ ምን እናገኛለን ብሎ ቢጠይቀው ፦ ሰው በሆንኩ ጊዜ የተከተላችሁኝ እናንተ ወልደ እጓለ እምህያው ክርስቶስ በጌትነቱ ዙፋን በተቀመጠ ጊዜ እናንተም በ12 ወንበሮች ተቀምጣችሁ በ12 ነገደ እስራኤል እንድትፈርዱ እውነት እላችኅለሁ ፡ ብሎ የፍርድ ተካፋዮች አድርጓቸዋል፡፡(ማቴ 19÷16) ከዚህም እልፍ ብሎ ያዘዝኳችሁን ሁሉ ከሰራችሁ ወዳጆቼ እላችኅለሁ እንጂ ባሮቼ አልላችሁም ፡ ባርያ ጌታው የሚያደርገውን አያውቅም ለናንተ ግን ካአባቴ የሰማሁትን ነግሬአችኅለሁ አስተምሬአችኅለንና ወዳጆቼ እላችኅለሁ እንጂ ባሮቼ አልላችሁም፡፡ ይህንኑም እኔ በሄድኩበት መንገድ ሔዳችሁ ለአለም የሚኖር ፍሬ ታፈሩ ዘንድ እኔ መርጨ ሾምኳችሁ እንጂ እናንተ የመረጣችሁኝ አይደላችሁም ብሎ ከግብርናተ ዲያቢሎስ ነፃ ከማውጣቱ በላይ አግብርተ ክርስቶስ መባል የክብር ክብር ሲሆን ባሮቼ አልላችሁም ወዳጆቼ እላችኅለሁ በማለቱ የበለጠ የባለሟልነት ማእረግ ሰጥቷቸዋል፡፡ (ዮሐ 14÷17) እንዲሁም “በዚያን ቀን በስሜ ትለምናላችሁ፤ እኔም ስለ እናንተ አብን እንድለምን የምላችሁ አይደለሁም”(ዮሐ.16÷26) ብሎ የእግዚአብሔር ባለሟሎች መሆናቸውን አረጋግጦላቸዋል፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሆኖ “አምላኬ አምላኬ ስለምን ተውከኝ” ባለው ጊዜ ዲያቢሎስ ሩቅ ብእሲ(ሰው) መስሎት በሌሎች እንደለመደ ነፍሱን ከስጋው ለይቶ ስጋውን በመቃብር ነፍሱን በሲኦል ሊቆራኝ ቀረበ፡፡በዚህ ጊዜ ምስጢረ መለኮቱን ብልጭ ቢያደርግበት መላእክት በመስቀሉ ዙርያ ወድቀው ክርስቶስን ሲያመሰግኑት አይቶ ፈራ ደነገጠ ሾልኬ አመልጣለሁ ብሎ ቢቃጣ በነፋስ አውታር በእሳት ዛንጅር አሰረው፡፡በዚህ ጊዜ ሰው ሆኖ ስጋ ለብሶ ድል የነሳኝ ምእመናንን ይነጥቀኝ ዘንድ ስልጣን የተሰጠው ይህ ማነው? ከኔ ህግ ልዩ የሆነ ነፍሳትን ከእኔ እጅ እየማረከ የሚወስድ ይህ ማነው? እንደ ሃጢአተኛ በመስቀል ተሰቅሎ ያለሃጢአት ሞቶ የወደድኩትን እንዳላደርግ የከለከለኝ ልቀርበው የማይቻለኝ ይህ ማነው?ለካስ ሳላውቀው ነው እንጂ እርሱስ ሰማያዊ ነው እያለ ቀባጠረ፡፡ ከዚህ በኋላ ጌታ ነቢያት የተናገሩት ነገር እኔም ሰው የሆንኩበት ምስጢር እንዲህ ዲያቢሎስን ለማሰር ነው፡፡ እነሆ ሁሉ ተፈፀመ ብሎ ክብርት ነፍሱን ከክብርት ስጋው በገዛ ስልጣኑ ለየ፡፡ (ዮሐ 19÷30) በአካለ ነፍስም ከአዳም እስከ ክርስቶስ ያሉ ነፍሳት ታስረው ተግዘው ወደነበሩባት ወደ ሲኦል ወርዶ ግእዛንን ሰበከላቸው ፡ ከቁራኝነት አስለቀቃቸው ወደ ቀደመ ቦታችው ወደ ገነት መለሳቸው፡፡ (1ጴጥ 3÷20)በአፀደ ስጋ ላሉ ሐዋርያትም በዝግ ቤት ገብቶ ቸር አላችሁን? የምስራች አስታረቅኳችሁ አላቸው፡፡ (ሉቃ 24÷36 ዮሐ 20÷20) ፤ 50 ቀን መፅሃፈ ኪዳንን አስተማራቸው፡፡(ሉቃ 24÷25) አብ እኔን ወደዚህ አለም እንደላከኝ እኔም እናንተን ወደአለም እልካችኅለሁና ፡ መንፈስ ቅዱስን በንፍሐት አሳደረባቸው፡፡ እናንተ ይቅር ያላችሁት ሃጢአቱ ይሰረይለታል ፡ ይቅር ያላላችሁት ሃጢአቱ አይሰረይለትም ብሎ በአንብሮተ እድ እስከ ሊቀጳጳስነት ያለውን ማእረግ ሾሟቸው አረገ፡፡(ዮሐ 20÷21 -24) እነዚህ ሁሉ ነገሮች እስከ መስቀል ድረስ ብቻ ናቸው ፡፡ በአጠቃላይ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰራው እስከ መስቀል የአማላጅነት ስራ ተገብቶ ነው አዳም ከተፈጠረ ግዜ ጀምሮ ሰዎች የሚፈልጉትን ካሣ በመክፈል ስለ ሰው ልጆች ተገብቶ የሚጸልይ የሚለምን የሚማልድ የሚያለቅስ በመጨረሻም ራሱን መስዋዕት አድርጎ በማቅረብ ጌታችን የሰራው ስራ አስታራቂነት ወይም አማላጅነት እንለዋለን፡፡ ይህ ስራ ከዚህ በፊት ያልተፈጸመ ከዛ ቦሃላ የማይደረግ አንድ ግዜ ብቻ የተደረገ ነው፡፡ አንድ ግዜ ካልን ቀራኒዎ ላይ ብቻ ነው ከትንሳኤ ቦሃላ አይከተለውም ከመስቀል ቦሃላ አያማልድም፡፡ ዛሬ ኢየሱስ ክርስቶስ(ከመስቀል ቦኋላ) እንደማያማልድ የመጽሐፍ ቅዱስ ማረጋገጫ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው የሆነበት ምክኒያት በምክረ ሰይጣን ተታሎ በኃጢአቱ ተጎሳቁሎ ኃይሉ ደካማ ሆኖ ተፈርዶበት በመንፈሰ ደይን ወድቆ የነበረ አዳምን ስጋ ለብሶ በበደለው በደል ሁሉ ክሶ የረከሰውን ቀድሶ ያረጀውን አድሶ ኃይሉን መልሶ ፀሎቱ ተሰሚ ተዋግቶ ድል እንዲነሳ አደረገው፡፡ ከማህበረ መላእክት ጨመረው፡፡ በክርስቶስ ካሳ መሆን ይህን ስልጣን ካገኘ በኃላ ያ ተዋርዶ በመንፈስ ደይን(ሲኦል) ወድቆ ጽድቃችን እንደ መርገም ጨርቅ ሆነ ይል የነበረ ሰው ጸሎቱ መስዋዕት ጉዳይ ፈፃሚ ስለሆነለት ቅዱስ ጳውሎስ "እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ። እንግዲህ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማለድ ስለ ክርስቶስ መልክተኞች ነን፤ ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን ስለ ክርስቶስ እንለምናለን።" 2ኛ ቆሮ 5÷20 ኢየሱስ ክርስቶስ በራሱ አንደበት ከመስቀል በኋላ ልመና(ምልጃ) ማስታረቅ እንደማይፈፅም ሲያረጋግጥ"በዚያን ቀን በስሜ ትለምናላችሁ(ትማልዳላችሁ) ፤ እኔም ስለ እናንተ አብን እንድለምን(እንደምማልድ) የምላችሁ አይደለሁም"የሐ 16÷26 በዚያን ቀን እያለ ለደቀ መዛሙርቱ የነገራቸው ከትንሳኤ በኋላ ያለውን ግዜ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በበኩሉ "ስለዚህ እኛ ከአሁን ጀምሮ ማንንም በሥጋ እንደሚሆን አናውቅም፤ ክርስቶስንም በሥጋ እንደ ሆነ ያወቅነው ብንሆን እንኳ፥ አሁን ግን ከእንግዲህ ወዲህ እንደዚህ አናውቀውም።" 2ኛ ቆሮ 5÷16-17 ቅዱስ ጳውሎስ ክርስቶስን በስጋው ጾሞአል(ማቴ 4÷1) በስጋው ተርባል(ማር 11÷12) በስጋው ጸልዩአል(ማቴ 26÷36) በስጋው መከራን ተቀብላል(ዕብ 13÷12) በስጋው ማልዶናል(ኢሳ 53÷12) … ወዘተ ያወቅነው ብንሆንም ከዚህ በኋላ ግን እንዲህ በለ ሁኔታ አናውቀውም አለ፡፡ ምልጃም አከተመ አያማልድም የምንለው ቅዱስ ጳውሎስ አስተምሮን ነው ፡፡ "እንደዚህ ያለ ሊቀ ካህናት ይገባልና፤ እርሱም እንደነዚያ ሊቃነ ካህናት አስቀድሞ ስለ ራሱ ኃጢአት በኋላም ስለ ሕዝቡ ኃጢአት ዕለት ዕለት መሥዋዕትን ሊያቀርብ አያስፈልገውም፤ ራሱን ባቀረበ ጊዜ ይህን አንድ ጊዜ ፈጽሞ አድርጎአልና። ዕብ 7÷26-27" አንድ ግዜ ነው የሚለው፡፡ "ሊቀ ካህናትም በየዓመቱ የሌላውን ደም ይዞ ወደ ቅድስት እንደሚገባ፥ ራሱን ብዙ ጊዜ ሊያቀርብ አልገባም፤ እንዲህ ቢሆንስ፥ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ብዙ ጊዜ መከራ ሊቀበል ባስፈለገው ነበር፤ አሁን ግን በዓለም ፍጻሜ ራሱን በመሠዋት ኃጢአትን ሊሽር አንድ ጊዜ ተገልጦአል።" ዕብ 9÷25 አንድ ግዜ ነው የሚለው፡፡ "ሊቀ ካህናትም ሁሉ ዕለት ዕለት እያገለገለ ኃጢአትን ሊያስወግዱ ከቶ የማይችሉትን እነዚያን መሥዋዕቶች ብዙ ጊዜ እያቀረበ ቆሞአል፤ እርሱ ግን ስለ ኃጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ" ዕን 10÷11 ይታያችሁ አሁንም አንድ ግዜ ተብሎ ነው የታፃፈው፡፡ አሁን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አማላጅ አይደለም ፦ ስለምን ቢሉ 1) የሁሉ ነገር አስገኝ እርሱ ነውና - - አብ ሙታንን እንደሚያነሣ ሕይወትም እንደሚሰጣቸው፥ እንዲሁ ወልድ ደግሞ ለሚወዳቸው ሕይወትን ይሰጣቸዋል።ሰዎች ሁሉ አብን እንደሚያከብሩት ወልድን ያከብሩት ዘንድ፥ ፍርድን ሁሉ ለወልድ ሰጠው እንጂ አብ በአንድ ሰው ስንኳ አይፈርድም። ወልድን የማያከብር የላከውን አብን አያከብርም።(ዮሐ.5÷21 -22) - - - - ዮሐ.1:3 ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም። 2) ምህረትን የሚሰጥ እንጂ የሚለምን አይደለምና - - - ተአምራትን ሁሉ ሲያደርግ እንደ ነብያት “በእግዚአብሄር ስም “ ወይንም እንደ ሃዋርያት “በኢየሱስ ክርስቶስ ስም” አለዚያም “በቅድስት ስላሴ ስም” አላለም ፡ ሁሉን በስልጣኑ አደረገ እንጂ፡፡ 3) መራጭ እንጂ ተመራጭ አይደለም ፡ ሁሉን እንደመረጠ እሱ የሚመረጥ አይደለም ምክንያቱም ለእርሱ ክብሩም ሃብቱም የባህርይው ነውና - - - - ሉቃ6÷13 በነጋም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን ጠራ፥ ከእነርሱም አሥራ ሁለት መረጠ ደግሞም ሐዋርያት ብሎ ሰየማቸው - - - ዮሐ.15:16 እኔ መረጥኋችሁ እንጂ እናንተ አልመረጣችሁኝም፤ አብም በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ እንዲሰጣችሁ፥ ልትሄዱና ፍሬ ልታፈሩ ፍሬአችሁም ሊኖር ሾምኋችሁ። - - - ታዲያ የዛሬዎቹ ተረፈ ሉትራን ሳይበቁ በቅተናል ሳያቁ አውቀናል ብለው ዛሬም ኢየሱስ አማላጅ ነው ለማለት የሚቀቅሱትን ጥቅስ እንይ ፩ “ፀሎትንና ምልጃን አቀረበ” ዕብ.5:7 ሲል ምን ማለቱ ነው? እርሱም በስጋው ወራት ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር ጸሎትንና ምልጃን አቀረበ፥ እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት - -- ይህ ምን ማለት ነው? ይህ ጥቅስ በማያሻማ ሁኔታ የተገለፀው ነገረ ስጋዌ(እስከ መስቀል ድረስ)ነው፡፡ጌታችን ሊቀ ካህናት ተብሎ ነበርና በስጋው ወራት እንደ ካህናተ ኦሪት የበግና የፍየል ደም ያቀረበ አይደለም፡፡ይልቁንም ፀሎትን እንደላም ልመናንም እንደበግ አድርጎ አቀረበ፡፡ አንድ ጊዜም ስለሆነ ያቀረበው ግዳጅ የሚፈፀም መሆኑን ሲያጠይቅ “ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ” አቀረበ አለ፡፡ “ከሞት ሊያድነው ወደሚችል” ሲልም ሰው ሁሉ በአንድ አዳም እንደሞተና በጌታም በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት በኩል እንደዳነ ስለምእመናን በጌታችን መናገሩ ነው፡፡ “እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት” የሚለው “ወልድ” “በኩር” ሆኖ ሳለ አምላክነት ገንዘቡ ሆኖ ሳለ ፍፁም ሰው በመሆኑ ስለአዳም ያቀረበው ቁርጥ ልመናው ተሰማለት አምላክ ነኝ ልፅልይ አይገባኝም ሳይል ሰው በመሆኑ ታዝዟልና፡፡ ስለመታዘዙም እግዚአብሄርን ስለመፍራቱ ቢል አንድ ነው - - - በአዳም ተገብቶ ነው እንጂ ጌታችን ከመከራ መስቀል በኅላ የሚያማልድ ሆኖ አይደለም፡፡ ፪ "እኔ መንገድ እውነት ህይወት ነኝ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም " የሐ 14÷5 ዛሬ በእና ግቢ የተነሱ ልጆችን ከእውነት መስመር ለማስወጣት የሚራራጡ መናፍቃን ከአንደበታቸው የማትለይ ቃል ናት ከላይ ጀምረን ስናነበው ኢየሱስ እያስተማረ ያለው ስለ አማላጅነት ትምህርት ሳይሆን ከአብ ጋር ስላለው የባህሪ ህልውና እና ስለ መንግስተ ሰማያት አወራረስ ነው፡፡ ገና ሲጀምር ቁጥር 1 ለይ "በእግዚአብሔር እመኑ በእኔም ደግሞ እመኑ" ይላል ህይ ማለት በተለየ አካል በተገለጥኩት በወልድ(ክርስቶስ) በእኔም እመኑ ማለቱ ነው፡፡ ምክኒያቱም ወልድ(ኢየሱስ) ከአምላክነቱ ዝቅ ያለ መስሏቸው እንዳይሳሳቱ ከአብ ጋር በስልጣን በባህሪ አንድ ነውና በእኔም እመኑ አለ፡፡ ለዚህ ነው ወረድ ቁጥር 8 ላይ ብሎ "እኔን ያየ አብን አይቷል፡፡"ያለው በቀጣዩ ምዕራፍ ላይ "ለአብ ያለው ሁሉ የእኔ ነው " ያለው ከአብ ጋር ያለው የስልጣን አድነትን ለመግለጽ ነው፡፡ ቁጥር 2 ሲደርስ ደግሞ "በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ" ብሏል ይህ የሚያሳየው የነፍሳችን የደስታ ቦታ እንዳለች ነው፡፡ ምክኒያቱም በማቴ 13÷23 እንደምናነበው ሁሉም ሰው እኩል የነፍስ ቱሩፋት አይፈረጽምም ባለሰላሳ ባለስልሳ ባለመቶነ ፍሬ አለ፡፡ በአባቴ ብዙ መኖሪያ አለ ማለቱ እንደነ ቅዱስ እስጢፋኖስ እንደ ቅዱስ ጊዮርጊስ በተጋድሎ የፀኑ ምስክሮች የሚወርሱት ቦታ፡፡ እንደ አብርሃም እንግዳ ተቀባይ የሚወርሱት ቦታ፡፡ እንደ ሐዋርያት ወንጌልን ሰብከው ጽድቅ ተብሎላቸው የሚወርሱት ቦታ፡፡ ታዲያ ይችን የጽድቅ ቦታ ለመውረስ የእግዚአብሔር አምላክነት ጌትነት ገዚነት በተላይም መኖሩን ለማወቅ መንገዱ ኢየሱስ መሆኑን ለመግለፅ ፈልጎ ቁጥር 6 ላይ "እኔ መንገድ እውነት ህይወት ነኝ" አለ እንግዲ እናስተውል እኔ መንገድ ነኝ ያለው አማላጅ ማለቱ አይደለም ቁጥር 2 ላይ "ወደ ምሄድበትስ ታውቃላችሁ መንገዱንስ ታውቃላችሁ" በማለት ጌታ ለሐወርያት መንገዱን ብቻ ሳይሆን ስፍራውንም ጠየቃቸው ቶማስም "ጌታ ሆይ ወደምትሄድበት አናውቅም እንዴትስ መንገዱን እናቃለን "ነበር ያለው ልብ በሉ ሁለት ጥያቄ የያዘ ነው ፡፡ አንደኛ "ወደ ምትሄድበት አናውቅም " ስፍራውና የመጠየቅና ሁለተኛ ደግሞ "እንዴትስ መንገዱን እናቃለን" በማለት ኢየሱስ ወደሚሄድበት ስፍራ አለማወቅን ያስረዳል፡፡ ስፍራው ቅድም እንዳየንው የምንናፍቃት ተስፋ መንግስተ ሰማያት ናት፡፡ አሁን መንገዱስ ነው ጥያቄው ኢየሱስ ይሄድ የነበረው በየሐ 16÷5 መሰረት ወደ አብ ነው፡፡ በመሆኑም ቶማስ የምትሄድበትን(አብን) አናውቅም ባለው ግዜ አብን የትታውቀው በእኔ መንገድነት ነው ሲል" እኔ መንገድ ነኝ" አለ መንገድ በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተለያየ ትርጉም ቢኖረውም እዚህ ስፍራ ግን የአብ መታወቂያ(መገለጫ) ልጁ ነኝ ማለቱ ነው፡፡ በእርግጥም ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድስት ስላሴን ያወቅንበት እውነተኛ መንገድ ነው፡፡ ማለትም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ያወቅንበት መንገዳችን ነው ለምሳሌ በማቴ 3÷16 ላይ ሲጠመቅ "የምወደው ልጄ ይህ ነው" በማለቱ አብ አባትነቱ ታወቀ እህንን ሚስጥር ያወቅንው በኢየሱስ ክርስቶስ መንገድነት ነው፡፡ ቁጥር 6 ላይ ታዲያ" በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም"ማለቱ እኔን መንገዱን ሳያውቅ አብን የሚያቅ የለም ወይም እኔን ተወላዲ ሳያውቅ አብን ማወቅ አይችልም መሆኑን ገለፀላቸው፡፡ ቁጥር 7 ላይ ይህንን ሲያጠናክር "እኔንስ ብታቁኝ አባቴን ባወቃችሁት ነበር፡፡" ማለት ስፍራውን ያላወቁት መታወቂያውን ኢየሱስን አለማወቃቸው እንደሆነ ገለፀላቸው፡፡ እንግዲህ ከላይ በዝርዘር እንዳየንው መንገድ ማለት እንደ ሊፍት የሚያደርስ አይደለም አስተውሎ ምንባቡን ለተረዳው ቶማስ የጠየቀው ስፍራና መንገዱን ያለማወቅ ሁኔታ እንጂ የምልጃን ሁኔታ ፈፅሞ አያሳይም፡፡ ሌላው ከዚህ በጣም ልናስተውለው የሚገባው ነጥብ ጌታ አማላጅ ነው ከተባለ ህይወት ሰጪ እንዴት ሊሆን ይችላል፡፡ ምክኒያቱም አማላጅ ስራው ህይወትን ድህነትን ማሰጠት ነው እንጂ በራሱ አዳኝ አይደለም ኢየሱስ ግን እኔ ሕይወት ነኝ ብላል ስለዚህ አማላጅ ነው ካልን ከቃሉ ጋር እንጋጫለን፡ ፫ “ የአዲስ ኪዳን መካከለኛ “ ምን ማለት ነው? … ዕብ.12:24 የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ ከአቤልም ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር ወደ መርጨት ደም ደርሳችኋል… 1ጢሞ.2:5 አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው …ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብቸኛም እውነተኛም የሰውና የእግዚአብሄር መካከለኛ ነው፡፡ ለምን? 1) የነሳው ስጋ የሰው ነውና - - ክርስቶስ አምላክ የሆነ ሰው ፡ ሰውም የሆነ አምላክ ከእርሱ በቀር የለምና “መካከለኛ” የተባለ ወልደ እግዚአብሄር የነሳው ስጋ የሰው ስለሆነ ነው 2) በተዋህዶ አንድ አካል አንድ ባህርይ ሆኗልና - ማቴ 16:16 ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ፡- አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለ። በዚህም በፍፁም ተዋህዶ የሰውና የእግዚአብሄር እንደሆነ አወቅን፡፡ ክርስቶስም እንደሰውነቱ ዘመዳችን እንደአምላክነቱ ፈጣሪያችን በመሆኑ በሰውና በእግዚአብሄር መካከል ያለ መካከለኛ ተባለ፡፡ 3) የብሉይና የአዲስ ኪዳን መካከለኛ ስለሆነ ነው … በብሉይ የነበረው የላም የበግ - - - መስዋእት በሃዲስ ኪዳን ፍፁም በሚበልጠው በክርስቶስ ደም ተተክቷልና ለብሉይ ኪዳን ካህናትና ለሐዲስ ኪዳን ካህናት አገልግሎትም ሆነ የሹመት ስርአት ፡ ለክህነቱም የስልጣን ልዩነት መካከለኛው ክርስቶስ ነው ፡ ስለዚህም “መካከለኛ” ተባለ፡፡ ፬ "እነርሱም(የብሉይ ኪዳን ካህናት) እንዳይኖሩ ሞት ስለ ከለከላቸው ካህናት የሆኑት ብዙ ናቸው፤ እርሱ ግን ለዘላለም የሚኖር ስለሆነ የማይለወጥ ክህነት አለው፤ ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል።" ዕብ 7÷25 ቃሉን ለመረዳት በደንብ ገፀ ንባቡን እንመልከት ከዚህ ሁለት መሰረታዊ ነገሮችን ያሳየናል አሮንን ተከትለው የመጡ ሁሉም ካህናት ማች እንደሆኑ በእነሱ አገልግሎት ፈጽሞ ወደ እግዚአብሔር መንግስት መድረስ እንዳልቻሉ ያሳየናል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘላለማዊ ሞት የማያልፍ ክህነቱም የማይለወጥ በመሆኑ አንድ ግዜ ባቀረበው መስዋዕት ስንታረቅበት የምንኖር መሆኑን ያሳያል፡፡ ወንድሞቼ እህቶቼ እናስተውል የዕብራዉያን ጻሐፊ ከላይ እየገለፀ የመጣው የኦሪት ካህናትን አገልግሎት ምን እንደመሚመስል ነበር፡፡ የብሉይ ካህናት ከሌዊ ዘር ተመርጠው በየዕለቱ ድህተት መስዋዕት እናሉ ቢያርዱ ቢሰው የእለት መከራን እንጂ ዘላለማዊ የነፍስ ድህነት ሊያመጣ አልቻለም፡፡ ካህኑ እንካን የህዝቡን ኃጢአት ቀርቶ የራሱን እንካን የዘላለም ህይወት ማስገኘት አልቻለም፡፡ እንግዲህ ካህናት እያገለገሉ በምት ካህናት ሁሉም በሞት እየተነጠቁ እስከ ካህኑ ዘካርያስ በሞት ይነጠቁ ነበር "እነሱም እንዳይኖሩ ሞት ስለከለከላቸው ካህናት የሆኑ ብዙ ናቸው" ያለው ለዚህ ነው "እርሱ ግን ለዘላለም የማይለወጥ ክህነት አለው" የተባለው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፡፡ አለምን አሳልፎ ለዘላለም ህያው ሆኖ የሚኖር ኢየሱስ ነው "ኢየሱስ ትላንትና ዛሬ ዘላለም ያው ነው" ይላል ወንጌል ክህነቱ ከሰው የተገኘ ሳይሆን የባህርይ ገንዘቡ ስለሆነ ዘላለማዊ ካህን ነው፡፡ "እንደ መልከጸዴቅ ለዘላለም አንተ ካህን ነህ ተብሏል፡፡ ዕብ7÷17 ስለዚህ ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና አነርሱም የተባሉት እንዳይኖሩ ሞት የከለከላቸው የብሉይ ኪዳን ካህናትን እንጂ ዛሬ እኛን አይደለም ወንጌሉን መላልሰው ያንብቡት ነው መልሳችን፡፡ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ዛሬም ኢየሱስ እየወደቀ የእየተነሳ በሰማይ ያማልዳል ካሉ ሁለት ስህተቶችን ፈፅመዋል አንደኛው ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምድር የፈፀመው የማዳን ስራ ያላለቀ(incomplete) ነው ማለት ነው፡፡ ሁለተኛ ኢየሱስ ዕለት ዕለት መስዋዕት እያደረገ ያቀርባል ዕለት ዕለት ይፀልያል እንደማለት ነው ይህ ደግሞ ዘላለማዊ ክህነቱን ምድራዊ ብቻ ማድረግ ነው፡፡ወደ እውነት ተመለሱ መልክታችን ነው፡፡ ፭ የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው። ሮሜ 8÷34 አንድ ወጪ ወራጁን የሚያስጨንቁበት ጥቅስ ቢኖር ይህ ነው ልብ በሉ በ1938 የታተመው መፅሐፍ ቅዱስ ላይ ስለ እና የሚፈርደው እንዲሁም 1975 ከግዕዝ ወደ አማረኛ የተተረጎመውም እና የሚፈርደው አሁን ግን በአብዛኛው ህዝብ ዘንድ ያለው ስለ እና የሚማልደው ነው፡፡ እነዚህን 1938 እንዲሁም 1975 መጽሐፍ ቅዱስ በላይብረሪ ገብታችሁ ማንበብ ትችላላችሁ በሮሜ 8÷34 ላይ በተለያዩ ዘመናት የተጻፉ መፅሐፍት ስለ እኛ ይፈርዳል ብሎ ፈራጅ ሲያደርገው በብዝዎች እጅ ላይ የሚገኘው ደግሞ ትርጉሙ አማላጅ ይላል ታዲያ የቅዱስ ጳውሎስ ቃል የቱ ነው ትክክል፡፡ ቁጥር 33 እንዲህ ብሎ ይጀምራል" እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን ይከሳቸዋል?" ይላል ይህ የመምረጥ ስልጣን የሚያሳይ ነው ቀጥሎ ደግሞ "የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው፥ የሚኰንንስ(የሚፈርድ) ማን ነው?" በማለት ጥያቄ ይጠይቃል ኮነነ ማለት ሲኦል አስገባ ወይም ገነት አኖረ ማለት ነው፡፡ ይህ ደግሞ ፍርድን የመሚያሳይ እንጂ አማላጅነትን ፈፅሞ አይገልፅም፡፡ መኮነን የፈራጅነት ስራ መሆኑን መረዳት ይገባናል፡፡ የሚኮንነው ማነው ብሎ ለጥያቄው መልስ ሲሰጥ የሞተው ትክክል ነው የሚኰንነው ሞቷል፡፡ ይልቁኑ ከሙታን የተነሣው ይላል ሙሉ በሙሉ ትክክል ነው ከሙታን የሚኰንነው ኢየሱስ ተነስታል፡፡ ቀጥሎ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው መቼም እግዚአብሔር ቀኝና ግራ ኁላና ፊት የለውም የማይወሰን ረቂቅ ነው፡፡ ታዲያ የእግዚአብሔር ቀኝ ሲል ምን ማለት ነው በመጽሐፍ ቀኝ ኃይል ስልጣንን ያመለክታል በመዝ 117÷16 ላይ "እግዚአብሔር ቀኝ ኃይልን አደረገች " ግልፅ ነው የእግዚአብሔር ኃይሉን የሚያደርገው ሰዎችንን ከፍ ከፍ የሚያደርገው በስልጣኑ በመለኮታዊ ኃይሉ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔር ቀኝ ሲል ስልጣንን (መለኮታዊ ክብሩን) ያመለክታል፡፡ በመቀጠል እንዲህ ይላል ስለ እኛ ¬¬--------ክርስቶስ ኢየሱስ ነው ፡፡ ክፍት ቦታው ላይ ሙሉ ቢሉን ያለ ጥርጥር የምንሞላው የሚፈርደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው ብለን ነው፡፡ ምክኒያቱም ከላይ በዝርዝር እንዳየንው ፈራጅነቱን እንጂ አማላጅነቱን በፍጹም አያሳይም ቃሉ ወደዚህ ወደዛ አያረግም፡፡ ደግሞ "የሚኰንነው ማነው የሚለውና ስለ እኛ የሚማልደው የሚለው ሁለት ቃለት ይጣረሳለው ይጋጫሉ አስማምቶ መተርጎም ተገቢ ነው፡፡የእኛ 81 መጽሐፍ የሚፈርደው ብሎ ነው ያስቀመጠው፡፡እንግዲህ ወንድሞቼ እህቶቼ አሁን ኢየሱስ የሚወድቅ የሚነሳ የሚማልድ አይደለም ምክኒያቱም ቅዱስ ጳውሎስ 2ኛ ቆሮ 5÷16 " ክርስቶስንም በሥጋ እንደ ሆነ ያወቅነው ብንሆን እንኳ፥ አሁን ግን ከእንግዲህ ወዲህ እንደዚህ አናውቀውም።" ተብሎ ተቀምጣልና፡፡ ስለ ፈራጅነቱ ከቅዱሱ መጽሐፍ ማረጋገጫ ሲያርግ እሁን እሱ በክቡር ዙፋን ተቀምቆ የሚፈርድ ነው እንጂ፡፡ መጽሐፍ እንዲህ ይላል ሁላችን "በክርስቶስ ፍርድ ወንበር ፊት እንቆማለንና።"ሮሜ 14÷10 "በክርስቶስ በፍርድ ወንበር ፊት ልንገለጥ ይገባናልና።2ኛ ቆሮ 5÷10 "ፍርድን ሁሉ ለወልድ ሰጠው" ዮሐ 5÷22 "በእግዚአብሔር ፊት በሕያዋንና በሙታንም ሊፈርድ ባለው በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት፥ በመገለጡና በመንግሥቱም እመክርሃለሁ" 2ኛ ጢሞ 4÷1 "የሰው ልጅም ስለ ሆነ ይፈርድ ዘንድ ሥልጣን አለው።"የሐ5÷27 "ለሰው ፊትም ሳያደላ በእያንዳንዱ ላይ እንደ ሥራው የሚፈርደውን አባት ብላችሁ ብትጠሩ በእንግድነታችሁ ዘመን በፍርሃት ኑሩ።" 1ኛ ጴጥ1÷17 በመጨረሻም "ኢየሱስም፦ የማያዩ እንዲያዩ የሚያዩም እንዲታወሩ እኔ ወደዚህ ዓለም ለፍርድ መጣሁ አለ።" የዛሬዎቹ ተረፈ አይሁዳዉያንን ከታወሩበት ክህደት ያወጣቸው ዘንድ ኢየሱስ ጌታ ፈራጅ ገዚ ንጉስ አማላክ ብለው ይመሰክሩ ዘንድ ያብቃቸው አሜን፡፡
ታቦት ምንድነው? ለምንስ ለታቦት ይሰገዳል? ታቦት በማን ይሰራል?

ታቦት ምንድነው?

ታቦት ማለት ማደሪያ ማለት ነው። የማን ማደርያ ለሚለው ደግሞ የእግዚዓብሔር ማደሪያ ማለት ነው።
እንግዲ መልሳችንን ስንሰጥ ትክክለኛ ለመሆኑ ማረጋግርጫችን መጽሐፍ ቅዱስ በመሆኑ የተወሰኑ ስለታቦትየተጠቀሱ ጥቅሶችን እያየን ወደፊት እንሄዳለን። ኦሪት ዘጸአት 31-33 ብንመለከት ሙሴ የእስራዔልን ህዝብከግብጽ ምድር አውጥቶ ወደ ከነዓን ወደ አባቶቻቸው አገር እየወሰዳቸው ሳለ ብዙ ጊዜ ከእግዚዓብሔር ጋርእንደተነጋገረ ሁላችንም እናውቃለን። እንዲሁ ሙሴ ከእግዚዓብሔር ጋር ሊነጋገር ወደ ተራራ ወጣ።ተራራዉም ላይ ሲወጣ ህዝበ እስራኤልን ከተራራው በታች ትቶአቸው ነበር። ሙሴም ተራራው ላይ 40 ቀንእና 40 ለሊት ከእግዚአብሔር ጋር ሲነጋገር ቆየ። እግዚአብሄርም ለሙሴ አስርቱን ትዕዛዛት ጽላቶች ላይቀርጾ ሰጠው። እዚህ ጋር የመጀመሪያው ታቦት ቀራጭ እግዚአብሄር እንደሆነ መጽሃፍ ቅዱስ ይነግረናል። 

ጠቃሚ የሆኑ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅሶች 

ኦሪት ዘጸአት 3215 :-  ” ሙሴም ተመለሰ፥ ሁለቱንም የምስክር ጽላቶች በእጁ ይዞ ከተራራው ወረደጽላቶቹም በዚህና በዚያ በሁለት ወገን ተጽፎባቸው ነበር። ጽላቶቹም የእግዚአብሔር ሥራ ነበሩ ጽሕፈቱምበጽላቶች ላይ የተቀረጸባቸው የእግዚአብሔር ጽሕፈት ነበረ።
ኦሪት ዘጸአት 3218 :- ”እግዚአብሔርም ከሙሴ ጋር በሲና ተራራ የተናገረውን በፈጸመ ጊዜበእግዚአብሔር ጣት የተጻፈባቸውን ከድንጋይ የሆኑ ሁለቱን የምስክር ጽላቶች ሰጠው።
ክዚህም በኋላ ሙሴ ከተራራው ላይ ጽላቶቹን ከእግዚዓብሔር ተቀብሎ ሲወርድ ህዝበ እስራኤልእግዚዓብሔርኝ ክደው ጣዖት በጥጃ ምስል ሰርተው ለጣዖቱ ሲሰግዱ እና በጣዖቱ ፊት ሲጨፍሩ አይቶተናደደ ከእግዚዓብሔር የተቀበለዉን ጽላቶች ወደ ጣዖቱ እንደወረወረ እና ጽላቶቹ እንደተሰበሩ መጽሃፍቅዱስ ላይ ተጽፎአል።
ኦሪት ዘጸአት 32 19 :- ”ጥጃውንም ዘፈኑንም አየ የሙሴም ቍጣ ተቃጠለ፥ ጽላቶቹንም ከእጁ ጥሎከተራራው በታች ሰበራቸው የሠሩትንም ጥጃ ወስዶ በእሳት አቀለጠው፥ እንደ ትቢያም እስኪሆን ድረስፈጨው፥ በውኃውም ላይ በተነው፥ ለእስራኤልም ልጆች አጠጣቸው።
ታድያ የዘመኑ ጴንጤዎች ይቺን ጥቅስ በመያዝ። እግዚዓብሔር የሰራው ጽላት ተሰብሮአል ለዚ ታቦት ወይምሌላ ጽላት አያስፈልግም ይላሉ   መልሱ እንደሚከተለው ነው።
ኦሪት ዘጸአት 341 :-  ”እግዚአብሔርም ሙሴን አለው፦ ሁለት የድንጋይ ጽላቶች እንደ ፊተኞች አድርገህጥረብ በሰበርኻቸው በፊተኞቹ ጽላቶች የነበሩትን ቃሎች እጽፍባቸዋለሁ። ”
እናም ይህ ጥቅስ ሰዎች ጽላትን እንዲሰሩ እግዚዓብሔር ፍቃድ እንደሰጣቸው ይነግረናል። ሙሴምእንደተባለው አደረገ ሁለት ጽላቶችን ሰራ ወደተራራም ጽላቶቹን ተሸክሞ ወጣ እግዚአብሄርም በጽላቶቹላይ ከእንደገና አስርቱን ትእዛዛት ጻፈባቸው። ሙሴም ከተራራው ጽላቱን ተሸክሞ ሲወርድ ፊቱ ያንፀባርቅነበር። 
ኦሪት ዘጸአት 3429 :- ”እንዲህም ሆነ ሙሴ ከሲና ተራራ በወረደ ጊዜ ሁለቱ የምስክር ጽላቶች በሙሴእጅ ነበሩ ሙሴም ከተራራው በወረደ ጊዜ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ስለ ተነጋገረ የፊቱ ቁርበትእንዳንጸባረቀ አላወቀም ነበር።
ኦሪት ዘጸአት 34:30 :-  ”አሮንና የእስራኤልም ልጆች ሁሉ ሙሴን ባዩ ጊዜ፥ እነሆ የፊቱ ቁርበት አንጸባረቀወደ እርሱም ይቀርቡ ዘንድ ፈሩ።
የታቦትን ርዝመቱ ቁመቱን የወሰነዉም እግዚአብሄር እንደሆነ መጽሃፍ ቅዱስ ይነግረናል።
ኦሪት ዘጸአት 25:10-15 :-   እኔ እንደማሳይህ ሁሉ፥ እንደ ማደሪያው ምሳሌ እንደ ዕቃውም ሁሉ ምሳሌ፥እንዲሁ ሥሩት። ከግራር እንጨትም ታቦትን ይሥሩ ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል፥ ወርዱም አንድ ክንድተኩል፥ ቁመቱም አንድ ክንድ ተኩል ይሁን። በውስጥና በውጭም በጥሩ ወርቅ ለብጠው በእርሱም ላይበዙሪያው የወርቅ አክሊል አድርግለት። አራት የወርቅ ቀለበቶችም አድርግለት፥ እነርሱንም በአራቱ እግሮቹላይ አኑር በአንድ ወገን ሁለት ቀለበቶች፥ በሌላው ወገን ሁለት ቀለበቶች ይሁኑ። መሎጊያዎችንም ከግራርእንጨት ሥራ፥ በወርቅም ለብጣቸው። ለታቦቱ መሸከሚያ በታቦቱ ጐን ባሉት ቀለበቶች መሎጊያዎቹንአግባ። መሎጊያዎቹም በታቦቱ ቀለበቶች ውስጥ ይኑሩ፥ ከቶም አይውጡ።
 ኦሪት ዘጸአት 25:26:- ”በታቦቱም ውስጥ እኔ የምሰጥህን ምስክር ታስቀምጣለህ። ” እኔ የምሰጥህንመስክር ያለው ሁለቱን ጽላቶች ነው
የታቦት ጥቅም በኦሪት (ኢየሱስ ከመወለዱበፊት እግዚአብሄር ከህዝቡ ጋር ለመሆኑ ምልክት ነበር።በሃዲስ ኪዳን (ኢየሱስ ከተወለደባሗላለኢየሱስ ክርስቶስ የስጋው እና የደሙ ዙፋን በመሆን ያገለግላል።
ታቦት ባለበት እግዚአብሄር እና ሰው እንደሚገናኙ እግዚአብሄር እንዲ ሲል ለሙሴ ነግሮታል
ኦሪት ዘጸአት  25:21 :-  ”የስርየት መክደኛውንም በታቦቱ ላይ ታደርገዋለህ እኔም የምሰጥህን ምስክርበታቦቱ ውስጥ ታኖረዋለህ። በዚያም ከአንተ ጋር እገናኛለሁ የእስራኤልንም ልጆች ታዝዝ ዘንድ የምሰጥህንነገር ሁሉ፥ በምስክሩ ታቦት ላይ ባለው በሁለት ኪሩቤል መካከል፥ በስርየት መክደኛውም ላይ ሆኜእነጋገርሃለሁ።
የእግዚአብሄር ቁጣ በእስራኤላዊያን ላይ በመጣ ጊዜ ኢያሱም  ታቦት ፊት ሰግዶ እንደጸለየ መጽቅዱስይነግረናል።
መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 7:6 :- ”ኢያሱም ልብሱን ቀደደ፥ እርሱና የእስራኤልም ሽማግሌዎችበእግዚአብሔር ታቦት ፊት እስከ ማታ ድረስ በግምባራቸው ተደፉ በራሳቸውም ላይ ትቢያ ነሰነሱ። ኢያሱምአለ። ዋይ! ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ በአሞራውያን እጅ አሳልፈህ ትሰጠን ታጠፋንም ዘንድ ይህን ሕዝብዮርዳኖስን ለምን አሻገርኸውበዮርዳኖስ ማዶ መቀመጥን በወደድን ነበር እኮ!”

ታቦትን ጣዖት ነው ለሚሉ መልሳችን የሚከተለው ነው።

2 ቆሮንጦስ 616-17 :- ”ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ፤ ጽድቅ ከዓመፅ ጋር ምንተካፋይነት አለውና፧ ብርሃንም ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው? ክርስቶስስ ከቤልሆር ጋር ምንመስማማት አለው? ወይስ የሚያምን ከማያምን ጋር ምን ክፍል አለውየእግዚዓብሔር ታቦትንስ በጣዖትቤት የሚያኖር ማነው?” 
ይህን ጥቅስ የጴንጤዎቹ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ብናየው ” የእግዚዓብሔር ታቦትንስ በጣዖት ቤት የሚያኖር ማነው?”  የሚለዉን ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስም ከጣዖት ጋር ምን መጋጠም አለው? በሚል ቀይረውታል።
ሰዎች ታቦትን ይሰሩ ዘንድ ስልጣን የላቸዉም ለሚሉን መልሳችን የሚከተለው ነው::
ኦሪት ዘጸአት  37:1-9 :-
ባስልኤልም ከግራር እንጨት ታቦቱን ሠራ ርዝመቱም ሁለት ክንድ ተኩል፥ ወርዱም አንድ ክንድ ተኩል፥ ቁመቱም አንድ ክንድ ተኩል ነበረ። በውስጥም በውጭም በጥሩ ወርቅ ለበጠው በዙሪያውም የወርቅ አክሊል አደረገለት። አራት የወርቅ ቀለበቶችም አደረገለት እነርሱንም በአራቱ እግሮቹ ላይ አኖረ። በአንድ ወገን ሁለት ቀለበቶች፥ በሌላውም ወገን ሁለት ቀለበቶች ሆኑ መሎጊያዎቹንም ከግራር እንጨት ሠራ፥ በወርቅም ለበጣቸው። ታቦቱንም ለመሸከም በታቦቱ አጠገብ ባሉት ቀለበቶች መሎጊያዎቹን አገባ። ከጥሩ ወርቅም ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል፥ ወርዱም አንድ ክንድ ተኩል የሆነ የስርየት መክደኛ ሠራ። ሁለት ኪሩቤልንም ከተቀጠቀጠ ወርቅ ሠራ በስርየት መክደኛውም ላይ በሁለት ወገን አደረጋቸው። ከስርየት መክደኛውም ጋር አንዱን ኪሩብ በአንድ ወገን፥ ሁለተኛውንም ኪሩብ በሌላው ወገን አድርጎ በአንድ ላይ ሠራቸው። ኪሩቤልም ክንፎቻቸውን ወደ ላይ የዘረጉ ሆኑ፥ የስርየት መክደኛውንም በክንፎቻቸው ሸፈኑ፥ እርስ በርሳቸውም ተያዩ የኪሩቤልም ፊቶቻቸው ወደ መክደኛው ተመለከቱ።” 
ይህን ታቦት እንግዲ ሰው እንደሰራው መጽሐፍ ቅዱስባስልኤልም ከግራር እንጨት ታቦቱን ሠራይለናል::

ታቦት በኦሪት(ክርስቶስ ከመወለዱ በፊት ) እንጂ አሁን አይጠቅምም ለሚሉ መልሳችን የማቴዎስ ወንጌል 517ነው::
የማቴዎስ ወንጌል 517 :- ” እኔ ሕግንና ነቢያትን ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ልፈጽም እንጂ ለመሻር አልመጣሁም። እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይና ምድር እስኪያልፍ ድረስ፥ ከሕግ አንዲት የውጣ ወይም አንዲት ነጥብ ከቶ አታልፍምብሎአል ኢየሱስ ክርስቶስ::
ኦሪት ዘጸአት 27:21 :- ”አንተም መብራቱን ሁልጊዜ ያበሩት ዘንድ ለመብራት ተወቅጦ የተጠለለ ጥሩ የወይራ ዘይት እንዲያመጡልህ የእስራኤልን ልጆች እዘዛቸው። በመገናኛው ድንኳን ውስጥ በምስክሩ ታቦት ፊት ባለው መጋረጃ ውጭ አሮንና ልጆቹ ከማታ እስከ ማለዳ ድረስ በእግዚአብሔር ፊት እንዲበራ ያሰናዱትበእስራኤል ልጆች ዘንድ ለልጅ ልጃቸው የዘላለም ሥርዓት ይሁን ይህን ጥቅስ ስንመለከት ለልጅ ልጃቸው የዘላለም ሥርዓት ይሁን። እንጂ ለኦሪት (ኢየሱስ ክርስቶስ እስኪወለድ) ብቻ አይልም።

ዳዊትም ስለታቦት በመዝሙሩ እንዲህ ብሎአል
መዝሙረ ዳዊት  132:7-9 :- ”ወደ ማደሪያዎቹ እንገባለን እግሮቹ በሚቆሙበት ስፍራ እንሰግዳለን አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት። ካህናቶችህ ጽድቅን ይልበሱ

አንድ በእግዚአብሔር ስም የሚሰራ ቤት ታቦት ሊኖረው ይገባል።
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 22:19 :- ”አሁንም አምላካችሁን እግዚአብሔርን ትፈልጉ ዘንድ ልባችሁንና ነፍሳችሁን ስጡ ለእግዚአብሔርም ስም ወደሚሠራው ቤት የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳኑን ታቦትናየእግዚአብሔርን ንዋየ ቅድሳት ታመጡ ዘንድ ተነሥታችሁ የአምላክን የእግዚአብሔርን መቅደስ ሥሩ።

በሰማይም ታቦት እንዳለ የሚከተለውን በማለት ሐዋርያው ዮሐንስ በራእይ ያየውን ጽፎልናል
የዮሐንስ ራእይ11:19 :- ” በሰማይም ያለው የእግዚአብሔር መቅደስ ተከፈተ፥ የኪዳኑም ታቦት በመቅደሱ ታየ፥ መብረቅና ድምፅም ነጐድጓድም የምድርም መናወጥ ታላቅም በረዶ ሆነ።
ታቦተ ጽዮን ከሰራቻቸው ተአምራት አንድ አንዶቹ
የእግዚአብሔርን ታቦት መንካት የማይገባቸው ሰዎች አይነኩትም። ፍልስጤሞች እስራኤልን በጦርነት አሸንፈው ታቦተ ጽዮንን በማረኩ ወይም በወስዱ ጊዜ ታቦተ ጽዮን ላይ ጣዖታቸውንዳጎንንእንዳስቀመጡ እና ታቦተ ጽዮን ጣዖታቸዉን እንዳደቀቀች በመጽሃፍ ቅዱስ ተጽፎ እናገኛለን።
መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 5:1 - መጨረሻው :- ፍልስጥኤማውያንም የእግዚአብሔርን ታቦት ወሰዱ ከአቤንኤዘርም ወደ አዛጦን ይዘውት መጡ። ፍልስጥኤማውያንም የእግዚአብሔርን ታቦት ወስደው ወደ ዳጎን ቤት አገቡት በዳጎንም አጠገብ አኖሩት።በነጋውም የአዛጦን ሰዎች ማለዱ፥ እነሆም፥ ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት በምድር ላይ በግምባሩ ወድቆ ነበር ዳጎንንም አንሥተው ወደ ስፍራው መለሱት። በነጋውም ማለዱ፥ እነሆም፥ ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት በምድር ላይ በግምባሩ ወድቆ ነበር የዳጎንም ራስ እጆቹም ተቈርጠው በመድረኩ ላይ ወድቀው ነበር የዳጎንም ደረት ብቻውን ቀርቶ ነበር ስለዚህም የዳጎን ካህናት ወደ ዳጎንም ቤት የሚገቡት ሁሉ በአዛጦን ያለውን የዳጎንን መድረክ እስከ ዛሬ ድረስ አይረግጡም። የእግዚአብሔርም እጅ በአዛጦን ሰዎች ላይ ከበደች፥ አጠፋቸውም፥ አዛጦንንና ድንበራቸውንም በእባጭ መታቸው። የአዛጦንም ሰዎች እንዲህ እንደ ሆነ ባዩ ጊዜ። እጁ በእኛና በአምላካችን በዳጎን ላይ ጠንክራለችና የእስራኤል አምላክ ታቦት ከእኛ ዘንድ አይቀመጥ አሉ። ልከውም የፍልስጥኤማውያንን አለቆች ሁሉ ወደ እነርሱ ሰበሰቡና። በእስራኤል አምላክ ታቦት ምን እናድርግ? አሉ እርሱም፦ የእስራኤል አምላክ ታቦት ወደ ጌት ይዙር ብለው መለሱ። የእስራኤልንም አምላክ ታቦት ወደዚያ ተሸከሙት። ከተሸከሙትም በኋላ የእግዚአብሔር እጅ በታላቅ ድንጋጤ በከተማይቱ ላይ ሆነች ከታናሹም እስከ ታላቁ ድረስ የከተማይቱን ሰዎች መታ፥ እባጭም መጣባቸው የእግዚአብሔርንም ታቦት ወደ አስቀሎና ሰደዱት። የእግዚአብሔር ታቦት ወደ አስቀሎና በመጣ ጊዜ አስቀሎናውያን፦ እኛንና ሕዝባችንን ሊገድሉ የእስራኤልን አምላክ ታቦት አመጡብን ብለው ጮኹ። በከተማይቱ ሁሉ የሞት ድንጋጤ ነበርና፥የእግዚአብሔርም እጅ በዚያ እጅግ ከብዳ ነበረችና ልከው የፍልስጥኤማውያንን አለቆች ሁሉ ሰብስበው። የእስራኤልን አምላክ ታቦት ስደዱ፥ እኛንና ሕዝባችንን እንዳይገድል ወደ ስፍራው ይመለስ አሉ። ያልሞቱትም ሰዎች በእባጭ ተመቱ የከተማይቱም ዋይታ እስከ ሰማይ ወጣ።

ታቦተ ጽዮን ባህረ ዮርዳኖስን ለሁለት አንደከፈለች

 መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ  3:15-17 :-  ” እንዲህም ሆነ ሕዝቡ ዮርዳኖስን ሊሻገሩ ከየድንኳናቸው በወጡ ጊዜ፥ የቃል ኪዳኑን ታቦት የተሸከሙ ካህናት በሕዝቡ ፊት ይሄዱ ነበር። እንደ መከር ወራት ሁሉ ዮርዳኖስ እጅግ ሞልቶ ነበርና ታቦት ተሸካሚዎቹ ወደ ዮርዳኖስ ሲደርሱ፥ ታቦቱንም የተሸከሙት የካህናቱ እግሮች በውኃው ዳር ሲጠልቁ ከላይ የሚወርደው ውኃ ቆመ በጻርታን አጠገብ ባለችው አዳም በምትባል ከተማ በሩቅ ቆሞ በአንድ ክምር ተነሣ ወደ ዓረባ ባሕር ወደ ጨው ባሕር የሚወርደው ውኃ ፈጽሞ ተቋረጠ ሕዝቡም በኢያሪኮ ፊት ለፊት ተሻገሩ። የእግዚአብሔርንም የቃል ኪዳን ታቦት የተሸከሙ ካህናት በዮርዳኖስ መካከል በደረቅ መሬት ጸንተው ቆመው ነበር፥ ሕዝቡም ሁሉ ዮርዳኖስን ፈጽመው እስኪሻገሩ ድረስ እስራኤል ሁሉ በደረቅ መሬት ተሻገሩ።
መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 3:13 :- ” እንዲህም ይሆናል የምድርን ሁሉ ጌታ የእግዚአብሔርን ታቦት የተሸከሙ ካህናት እግር ጫማ በዮርዳኖስ ውኃ ውስጥ ሲቆም፥ ከላይ የሚወርደው የዮርዳኖስ ውኃ ይቋረጣል እንደ ክምርም ሆኖ ይቆማል።
አንድ ዖዛ የተባለ ካህን ያልሆነ ሰው ታቦት ሊነካ ሲል መቀሰፉን መጽሐፍ ቅዱስ ያስነብበናል::
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 13:9 :- ”ዳዊትና እስራኤል ሁሉ በቅኔና በበገና በመሰንቆና በከበሮ በጸናጽልና በመለከት በእግዚአብሔር ፊት በሙሉ ኃይላቸው ይጫወቱ ነበር። ወደ ኪዶንም አውድማ በደረሱ ጊዜ በሬዎቹ ይፋንኑ ነበርና ታቦቱን ሊይዝ ዖዛ እጁን ዘረጋ። የእግዚአብሔርም ቍጣ በዖዛ ላይ ነደደ፥ እጁንም ወደ ታቦቱ ስለ ዘረጋ ቀሠፈው በዚያም በእግዚአብሔር ፊት ሞተ።
አሁን ታድያ ይህቺ ተዓምረኛ ታቦት (ታቦተ ጽዮንበእግዚአብሄር ቅዱስ ፍቃድ  እስራኤል ወታ ወደ ቅድስት ሃገር ኢትዮጵያ እንደመጣች እና እስካሁነም ድረስ በኢትዮጵያ እንዳለች እስራኤላዊያን ሳይቀሩ ያውቃሉ።

የታቦት ክብር

ታቦት ባለበት እግዚአብሄር አለና፣ እግዚአብሄር በታቦቱ አድሮ ህዝቡን ይባርካልና ለታቦት ስግደት እና ክብር እንዲሁም ፍርሃት ይገባል። ታቦትን መዳፈር አይገባም።
ኦሪት ዘሌዋውያን 162 :-  ” እግዚአብሔርም ሙሴን አለው፦ እኔ በስርየቱ መክደኛ ላይ በደመናው ውስጥ እታያለሁና እንዳይሞት በመጋረጃው ውስጥ በታቦቱ ላይ ወዳለው ወደ ስርየቱ መክደኛ ወደ ተቀደሰው ስፍራ ሁልጊዜ እንዳይገባ ለወንድምህ ለአሮን ንገረው።

የእግዚአብሔርን መንበር የሚሸክሙ ኪሩቤል እና ሱራፌል በታቦትም አጠገብ እንዳሉ መጽሃፍ ቅዱስ ይነግረናል።
መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ 87:- ”ካህናቱም የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦት በቤቱ በቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ ከኪሩቤል ክንፍ በታች ወደ ነበረው ወደ ስፍራው አመጡት። ኪሩቤልም በታቦቱ ስፍራ ላይ ክንፎቻቸውን ዘርግተው ነበር ኪሩቤልም ታቦቱንና መሎጊያዎቹን በስተ ላይ በኩል ሸፍነው ነበር።መሎጊያዎቹም ረጃጅሞች ነበሩ በቅድስተ ቅዱሳን ፊት ከመቅደሱ ውስጥ ጫፎቻቸው ይታዩ ነበር በውጭ ያለ ግን አያያቸውም ነበር እስከ ዛሬም ድረስ በዚያ አሉ።
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 58:-  ” ካህናቱም የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦት ወደ ቤቱ አምጥተው በቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ ከኪሩቤል ክንፍ በታች በነበረው በስፍራው አኖሩት። ኪሩቤልም በታቦቱ ስፍራ ላይ ክንፎቻቸውን ዘርግተው ነበር፥ ኪሩቤልም ታቦቱንና መሎጊያዎቹን በስተ ላዩ በኩል ይሸፍኑ ነበር። መሎጊያዎቹም ረጃጅሞች ነበሩና በቅድስተ ቅዱሳን ፊት ከመቅደሱ ውስጥ ጫፎቻቸው ይታዩ ነበር ነገር ግን ከውጪ አይታዩም ነበር እስከ ዛሬም ድረስ እዚያ አሉ።
መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 34 :- ” በእናንተና በታቦቱ መካከል ያለው ርቀት በስፍር ሁለት ሺህ ክንድ ያህል ይሁን በዚህ መንገድ በፊት አልሄዳችሁበትምና የምትሄዱበትን መንገድ እንድታውቁ ወደ ታቦቱ አትቅረቡ ብለው አዘዙ።


 እነዚህን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች በርገጥ ብዙ ሰዎች እናውቀዋለን ግን በየዋህነት ይሁን በትእቢት ወይም በድፍረት አላውቅም ለታቦት ተገቢውን ክብር ስንሰጥ አይታይም።  እግዚአብሔር ልቦናዉን ሰጥቶን አምላካችንን እግዚአብሔርን ትእዛዝ ለመፈጸም ያብቃን! አሜን።